ጦርነት እና ግጭት የተለመዱ፤ ሰላም ቅንጦት ሆኗል - የጊኒ ባለሥልጣን
13:57 28.09.2025 (የተሻሻለ: 14:04 28.09.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ጦርነት እና ግጭት የተለመዱ፤ ሰላም ቅንጦት ሆኗል - የጊኒ ባለሥልጣን
በአንድ ወቅት በተባበሩት መንግሥታት ያስቀመጥነው ተስፋ በስጋት ተተክቷል ሲሉ ሚኒስትር ዴኤታው አማራ ካማራ ተናግረዋል። አክለውም ዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ ተቋማት እየተዳከሙ ነው ብለዋል።
ካማራ ያነሷቸው ተጨማሪ ቁልፍ ነጥቦች፦
▪ በአሁኑ ወቅት ዓለም የትኛውንም አህጉር ሳታስቀር ብጥብጥ ውስጥ መሆኗ ግልጽ ነው።
▪ ጊኒ ከአርብ ጀምሮ የዜጎቿን ፍላጎት የሚያንፀባርቅ እና አንድ የሚያደርግ ሕገ-መንግሥት አግኝታለች።
▪ ጊኒ የስታንዳርድ እና ፑርን የተረጋጋ ምልከታ ቢ ፕላስ (B+) በማግኘት በመጀመሪያው ሉዓላዊ ደረጃ ታሪካዊ ምዕራፍ አሳክታለች።
▪የሀገሪቱን ብሔራዊ እና የማዕድን ዘርፍ ሉዓላዊነት በማስቀደም ብሔራዊ የማዕድን ደንብን ጨምሮ ሕግና መመሪያን የጣሱ ተቋማትን ፍቃድ ሰርዛለች።
▪ጊኒ የሲማንዱ 2040 አጠቃላይ ፕሮግራምን እየተገበረች ነው። ይህም በአምስት ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች ላይ የተገነባ ነው፦
🟠 ግብርና፣ የምግብ ኢንስትሪ እና ንግድ፣
🟠 ትምህርት እና ባሕል፣
🟠 መሠረተ ልማት፣ ትራንስፖርትና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች፣
🟠 ኢኮኖሚ፣ ፋይናንስ እና ኢንሹራንስ፣
🟠 ጤና እና ደህንነት።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X