የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ በተመድ 80ኛ ጉባዔ ላይ ካደረጓቸው ንግግሮች፦

ሰብስክራይብ

የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ በተመድ 80ኛ ጉባዔ ላይ ካደረጓቸው ንግግሮች፦

🟠 ዛሬ ላይ የፍልስጤም መንግሥት ምስረታን በተመለከተ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ውሳኔን ለመቅበር የሚደረግ ሙከራን በተግባር እየተጋፈጥን ነው።

🟠 ለፍልስጤም እውቅና በሚሰጥበት ወቅት ምንም ዓይነት ግዛት እንዳይቀር የሚደረጉ ሙከራዎችን ለመከላከል አስቸኳይ እርምጃዎች መወሰድ አለባቸው።

🟠 ሩሲያ ምዕራባውያን የፀጥታው ምክር ቤት ማዕቀቦችን በኢራን ላይ መልሶ እንዲጥል የሚያደርጉትን ሙከራ ተቀባይነት የሌለውና ሕገ-ወጥ አድርጋ ትቆጥረዋለች።

🟠 ሩሲያ የዩክሬን ግጭት መንስኤዎችን ለመፍታት ለድርድር ዝግጁ ነች።

🟠 የሩሲያ ደህንነት እና ቁልፍ ጥቅም በአስተማማኝ ሁኔታ መረጋገጥ አለበት።

🟠 በዩክሬን ግዛቶች የሩሲያውያን እና የሩሲያኛ ተናጋሪ ሕዝቦች መብት ሊመለስ ይገባል።

🟠 ሩሲያ የኔቶ አባል ሀገራትን ለማጥቃት እቅድ የላትም፣ ነገር ግን ለማንኛውም ጥቃት የማያወላዳ አፀፋዊ ምላሽ ትሰጣለች።

🟠 ሞስኮ በቀጣይ የሩሲያ እና አሜሪካ ውይይት የዩክሬን ጉዳይ መፍትሄ እንደሚያገኝ ተስፋ ታደርጋለች።

🟠 ፑቲን በ 'ኒው ስታርት' ስምምነት ስር ገደቦችን ለማስቀመጥ ያቀረቡት ሃሳብ፤ የጦር መሳሪያ እሽቅድምድምን ለማስቀረት አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራል።

🟠 ሩሲያ የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት መሻሻልን ትደግፋለች፤ ማንም ላይ የተለየ ዘመቻ አታደርግም።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0