ኒጄር 'በመንግሥት የሚደገፍ ሽብርተኝነት' እየተጋፈጠች ትገኛለች - ጠቅላይ ሚኒስትር አሊ ማሃማን ላሚን ዜይን
19:04 27.09.2025 (የተሻሻለ: 19:14 27.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኒጄር 'በመንግሥት የሚደገፍ ሽብርተኝነት' እየተጋፈጠች ትገኛለች - ጠቅላይ ሚኒስትር አሊ ማሃማን ላሚን ዜይን
የሳህል ቀጣና የሽብር ተዋናዮች ከአካባቢው የሚነሱ አይደሉም ሲሉ የኒጄር ሽግግር መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር በተመድ 80ኛ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያነሷቸው ተጨማሪ ነጥቦች፦
▪በኢኮዋስ አማካኝነት የተካሄደው የወታደራዊ ጣልቃ ገብነት ማስፈራሪያ በፈረንሳይ የተደገፈ ነው።
▪ኒጄራውያን የቅኝ ግዛት ዘመን ጭካኔን አይረሱም።
▪ኒጄር የሕዝቦቿን ጥቅም የማያስጠብቁ ሁሉንም ውሎች አቋርጣለች።
▪በምዕራባውያን ኃይሎች የበላይነት የተደናቀፈውና ውጤታማ መሆን ያልቻለው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መሻሻል አለበት።
▪የኒጄር መንሳሳት ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር መለያየት ሳይሆን፤ "ሉዓላዊነታችንን፣ ክብራችንን እና ለትውልዶቻችን ደህንነት አጋርነታችንን የመምረጥ የማይገረሰስ መብታችንን የሚያረጋግጥ ነው።"
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X