የኢትዮጵያን የዓለም ንግድ ድርጅት የመቀላቀል ፍላጎት 30 ሀገራት ደገፉ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያን የዓለም ንግድ ድርጅት የመቀላቀል ፍላጎት 30 ሀገራት ደገፉ
የኢትዮጵያን የዓለም ንግድ ድርጅት የመቀላቀል ፍላጎት 30 ሀገራት ደገፉ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 27.09.2025
ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያን የዓለም ንግድ ድርጅት የመቀላቀል ፍላጎት 30 ሀገራት ደገፉ

በስዊዘርላንድ ጄኔቫ በተካሄደው የዓለም አቀፉ ንግድ ድርጅት 6ኛ የሥራ ቡድን ስብሰባ ላይ ለተነሱ ከ200 በላይ ጥያቄዎች በቂ ምላሽ መሰጠቱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ አስታውቀዋል።

በ5ኛው የሥራ ቡድን ስብሰባ ከ19 አባል ሀገራት ለኢትዮጵያ ድጋፍ መስጠታቸውን ያወሱት ሚኒስትሩ፤ በ6ኛው ዙር ድጋፋቸውን ያሳዩ ሀገራት ቁጥር ወደ 30 ማደጉን ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ጥያቄ ካቀረበች ከ20 ዓመታት በላይ ከፈጀ ሂደት በኋላ ለአባልነት መቃረቧን ጠቁመዋል።

"በቀጣይም ትጋትና ርብርባችንን አጠናክረን በመቀጠል የባለብዙ ወገንና የሁለትዮሽ የገበያ ዕድል ድርድሮችን የምናከናውን ይሆናል" ሲሉም ተናግረዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0