ለእኔ ዘመናዊነት ራስን መሆን ነው - መላኩ በላይ

ሰብስክራይብ

ለእኔ ዘመናዊነት ራስን መሆን ነው - መላኩ በላይ

የፈንድቃ ባሕል ማዕከል መሥራች ዳይሬክተሩ ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር በነበረው ቆይታ፤ ባሕላዊ ውዝዋዜ ኢትዮጵያን በምልዓት ከመተረክ ባለፈ ለሀገሪቱ ከፍተኛ የገቢ ምንጭ የመሆን አቅም እንዳለው ገልጿል።

ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ በማስተዋወቅ ላይ የሚገኘው የባሕል አምባሳደሩ፤ የውዝዋዜ ፍላጎት እና ተሰጥኦ ያላቸው ወጣቶችን በስፋት ወደ ፊት ለማምጣት በቅንጅት መሥራት እንደሚገባም አንስቷል።

"ባሕላዊ ውዝዋዜ እውነተኛ ማንነትን ማሳያ ነው። በውዝዋዜ የሕዝቡን አለባበስ፣ አመጋገብ፣ አኗኗር እና አስተሳሰብ ታሳያለሽ። ይህ አቅም ያላቸው ወጣቶች ላይ መዋዓለ ነዋይ ማፍሰስ ይገባል። ስልጣኔ ማንነትን ማክበር ነው" ብሏል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0