የመስቀል ደመራ በዓል የአከባበር ሥነ-ሥርዓት በመስቀል አደባባይ መካሄድ ጀምሯል
14:53 26.09.2025 (የተሻሻለ: 14:54 26.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የመስቀል ደመራ በዓል የአከባበር ሥነ-ሥርዓት በመስቀል አደባባይ መካሄድ ጀምሯል
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክስርስትያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ የአከባበር ሥነ-ሥርዓቱን በጸሎት አስጀምረዋል።
በደመራ በዓል የኢኦተቤ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስን ጨምሮ የቤተ-ክርስቲያኒቱ አባቶች፣ የየደብሩ ሊቃውንቶች፣ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት፣ ምሁራን፣ ምዕመናንና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በመስቀል አደባባይ እየተካሄደ ያለውን የመስቀል ደመራ በዓል ዝግጅት እየተከታተልን የምናደርስ ይሆናል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

