ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የኑክሌር ልማት ፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረሙ
21:07 25.09.2025 (የተሻሻለ: 23:14 25.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የኑክሌር ልማት ፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረሙ
ሩሲያ እና ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ልማት ዙሪያ በሮሳቶም እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን መካከል የድርጊት መርሃ ግብር ተፈራረመዋል።
የሮሳቶም ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሌክሲ ሊካቼቭ እና የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ፣ ቭላድሚር ፑቲን እና ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት የተፈረመውን ሰነድ ተለዋውጠዋል።
የፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ በክሬምሊን የመጀመሪያ ሕንጻ በሚገኘው የተወካይ ጽሕፈት ቤት በሩሲያው መሪ እና በኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር መካከል የተደረገው ውይይት አካል ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X