https://amh.sputniknews.africa
አፍሪካ በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ውስጥ ትልቅ ድምፅ ሊኖራት ይገባል ሲሉ የጋናው ፕሬዝዳንት አሳሰቡ
አፍሪካ በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ውስጥ ትልቅ ድምፅ ሊኖራት ይገባል ሲሉ የጋናው ፕሬዝዳንት አሳሰቡ
Sputnik አፍሪካ
አፍሪካ በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ውስጥ ትልቅ ድምፅ ሊኖራት ይገባል ሲሉ የጋናው ፕሬዝዳንት አሳሰቡ ጆን ማሃማ በተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ሲናገሩ "የተመድ ሚናውን እንደገና መገምገም፣ ይዘቱን እንደገና መወሰን እና መዋቅሮቹን እንደገና መቅረጽ... 25.09.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-09-25T20:40+0300
2025-09-25T20:40+0300
2025-09-25T20:44+0300
sputnik africa
telegram sputnik_ethiopia
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/img/07e9/09/19/1695926_0:0:1280:720_1920x0_80_0_0_d48b1e0e85c9436f20b4e8b097e6b064.jpg
አፍሪካ በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ውስጥ ትልቅ ድምፅ ሊኖራት ይገባል ሲሉ የጋናው ፕሬዝዳንት አሳሰቡ ጆን ማሃማ በተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ሲናገሩ "የተመድ ሚናውን እንደገና መገምገም፣ ይዘቱን እንደገና መወሰን እና መዋቅሮቹን እንደገና መቅረጽ አለበት" ብለዋል።ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ ዓለም አቀፉ ድርጅት "የዓለማችንን ኅብረ ብሄራዊ ልዩነት በትክክል ማንጸባረቅ" እንዲሁም በሥልጣን አጠቃቀም ላይ በተለይም በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ "በአገሮች መካከል እኩልነትን" ማረጋገጥ አለበት ብለዋል። ከሠላሳ ዓመታት በፊት ተመሳሳይ ጥሪዎች ከተደረጉ በኋላም ዛሬም "እኛ የአፍሪካ መሪዎች በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ የቬቶ (ድምጽን በድምጽ የመሻር) ሥልጣን ያለው ቋሚ መቀመጫ እንዲኖረን ተመሳሳይና ቀላል ጥያቄ አሁንም እያቀረብን ነው" ሲሉ ማሃማ የነገሩን ተመሳሳይነት ገልፀዋል። "ስለዚህ ዛሬ እዚህ በተከበረው ቦታ ቆሜ ክብርት ፕሬዝዳንት፤ ዓለምን 'አሁን ካልሆነስ መቼ ነው?' ብዬ እጠይቃለሁ" ሲሉ ተናገረዋል። "እኛ የምንፈልገው የፀጥታው ምክር ቤት ማሻሻያ ብቻ ሳይሆን፣ በአሁኑ ጊዜ አፍሪካን በሚጎዳ መልኩ የተደራጀውን የዓለም አቀፉ የፋይናንስ መዋቅርም እንደገና እንዲከለስ ጭምር ነው።" በማለት አጽናኦት ሰጥተዋል፡፡ በእንግሊዘኛ ለማንበብ ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
2025
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/img/07e9/09/19/1695926_160:0:1120:720_1920x0_80_0_0_602b7d094f79645d1b568f928d6726ee.jpgSputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
sputnik africa, telegram sputnik_ethiopia
sputnik africa, telegram sputnik_ethiopia
አፍሪካ በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ውስጥ ትልቅ ድምፅ ሊኖራት ይገባል ሲሉ የጋናው ፕሬዝዳንት አሳሰቡ
20:40 25.09.2025 (የተሻሻለ: 20:44 25.09.2025) አፍሪካ በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ውስጥ ትልቅ ድምፅ ሊኖራት ይገባል ሲሉ የጋናው ፕሬዝዳንት አሳሰቡ
ጆን ማሃማ በተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ሲናገሩ "የተመድ ሚናውን እንደገና መገምገም፣ ይዘቱን እንደገና መወሰን እና መዋቅሮቹን እንደገና መቅረጽ አለበት" ብለዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ ዓለም አቀፉ ድርጅት "የዓለማችንን ኅብረ ብሄራዊ ልዩነት በትክክል ማንጸባረቅ" እንዲሁም በሥልጣን አጠቃቀም ላይ በተለይም በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ "በአገሮች መካከል እኩልነትን" ማረጋገጥ አለበት ብለዋል።
ከሠላሳ ዓመታት በፊት ተመሳሳይ ጥሪዎች ከተደረጉ በኋላም ዛሬም "እኛ የአፍሪካ መሪዎች በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ የቬቶ (ድምጽን በድምጽ የመሻር) ሥልጣን ያለው ቋሚ መቀመጫ እንዲኖረን ተመሳሳይና ቀላል ጥያቄ አሁንም እያቀረብን ነው" ሲሉ ማሃማ የነገሩን ተመሳሳይነት ገልፀዋል።
"ስለዚህ ዛሬ እዚህ በተከበረው ቦታ ቆሜ ክብርት ፕሬዝዳንት፤ ዓለምን 'አሁን ካልሆነስ መቼ ነው?' ብዬ እጠይቃለሁ" ሲሉ ተናገረዋል። "እኛ የምንፈልገው የፀጥታው ምክር ቤት ማሻሻያ ብቻ ሳይሆን፣ በአሁኑ ጊዜ አፍሪካን በሚጎዳ መልኩ የተደራጀውን የዓለም አቀፉ የፋይናንስ መዋቅርም እንደገና እንዲከለስ ጭምር ነው።" በማለት አጽናኦት ሰጥተዋል፡፡
በእንግሊዘኛ ለማንበብ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X