ግልጽነት የጎደለውና ኢ-ፍትሐዊው የዓለም ባንክ አካሄድ

ግልጽነት የጎደለውና ኢ-ፍትሐዊው የዓለም ባንክ አካሄድ
ሰብስክራይብ
‘‘[ለአፍሪካ] ገንዘብ ሲያቀርቡ ለጽድቅ አይደለም፡፡ ፖሊሲን በማስቀየርና [...] ይህንንም እንደአንድ መግቢያ አድርጎ በሀገራቱ ውስጥ ያሉ ሚስጥራዊ የሆኑ ተቋማትንና ሀገራዊ ሚስጥሮችን ማግኛ አድርገው [ለመጠቀም ነው]፡፡ ይህንም ለፖለቲካ ፍጆታ በመጠቀም ሀገር ራሷን እንዳትችል ፣ ጥገኛ እና በእነሱ እንድትመራ ለማድረግ ይጠቀሙበታል፡፡ [...] ስለዚህ የብድር አሰጣጡ ወደአፍሪካ ሲመጣ ጥብቅ ነው ነገር ግን እነሱ ወደሚያስተዳድራቸው አሻንጉሊት መንግስታት ባሉበት አካባቢ ፍጹም ተቃራኒ ነው፡፡ ለዚህ ዩክሬንን በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል፡፡ ለአፍሪካ ከተሰጠው የገንዘብ ድጋፍ አንጻር ለዩክሬን የተሰጠው የገንዘብ ድጋፍ በ10 እጥፍ መብለጡም ለዚህ ነው፡፡’’
በዚህ የሜይን ስቴጅ ዝግጅታችን ሁለት የተለያዩ ግን ደግሞ ወሳኝ ጉዳዮች ላይ ሲያጠነጥን የአለም ባንክ ለአፍሪካ የሚሰጠው በመስፈርቶች የታጠረ ብድርና ለአካባቢን ንጽህና ሀገር በቀል ልምዶች ያላቸውን አበርክቶ በሰፊው ይዳስሳል፡፡ ለዚህም የፊስካልና የክልሎች ተመጣጣኝ እድገትና ሀብት ከፍተኛ ተመራማሪ ተድላ ኤልያስ እና የአዲስ አበባ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ም/ ዋ/ ዳይሬክተር ታከለ ዴሲሳን አነጋግረናቸዋል፡፡
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ AfripodsDeezerPocket CastsPodcast AddictSpotify
አዳዲስ ዜናዎች
0