ደቡብ አፍሪካ በቅኝ ገዥዎች የተወሰዱባት የሰው ቅሪተ አካላት እንዲመለሱላት ጠየቀች
20:50 24.09.2025 (የተሻሻለ: 20:54 24.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ደቡብ አፍሪካ በቅኝ ገዥዎች የተወሰዱባት የሰው ቅሪተ አካላት እንዲመለሱላት ጠየቀች
በደቡብ አፍሪካ የመልሶ ማቋቋም እና ካሳ ፕሮግራም አማካኝነት በዓለም ዙሪያ የሚገኙ እና ያለምንም መዘግየት ወደ ሀገሪቱ መመለስ ያለባቸውን የተቀደሱ የሰዎች ቅሪተ አካላት የያዙ ተቋማትን መለየቷን የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ፖል ማሻቲሌ በዓለም ቅርስ ቀን ንግግራቸው አንስተዋል።
ማሻቲሌ መንግሥታቸው የአፍሪካን የቅርስ ክብር ለመመለስ እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። አክለውም የአፍሪካን የባህል ልምምዶች በተደራጀ መልኩ የጣሰው እና ያወደመው የቅኝ ግዛት እና የአፓርታይድ ቅርስን ለመጋፈጥ እንዲሁም ለውጡን ለማፋጠን እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጥሪ አቅርበዋል።
በደቡብ አፍሪካ ስፖርት፣ ሥነ-ጥበብ እና ባህል ሚኒስቴር መሰረት፤ በቅኝ ገዥ ባለስልጣናት፣ ሰብሳቢዎች፣ ሳይንቲስቶች እና ሚስዮናውያን ለሁለት ክፍለ ዘመናት ያህል በዋናነት የሳን (ቡሽመን) እና ሌሎች የአገሬው ተወላጆች የራስ ቅሎች፣ አጥንቶች እና ሙሉ አጽሞች ጨምሮ በሺዎች የሚቆጠሩ የሰው ቅሪተ አካላት ከደቡብ አፍሪካ ተወስደዋል።
እነዚህ ቅሪተ አካላት በአሁኑ ጊዜ በእንግሊዝ፣ በጀርመን፣ በኔዘርላንድስ እና በፈረንሳይ በሚገኙ ሙዚየሞች እና የምርምር ተቋማት ውስጥ ይገኛሉ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X