ብሪክስ በምዕራባውያን ለሚመሩ ተቋማት የተለየ አማራጭ ያቀርባል ሲሉ ፕሮፌሰሩ ተናገሩ
20:58 22.09.2025 (የተሻሻለ: 21:04 22.09.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ብሪክስ በምዕራባውያን ለሚመሩ ተቋማት የተለየ አማራጭ ያቀርባል ሲሉ ፕሮፌሰሩ ተናገሩ
እንደ ዓለምአቀፉ የገንዘብ ተቋም እና የዓለም ባንክ ያሉ የብሬተን ዉድስ ተቋማት ድህነትን የሚጭኑ እና ያለምርጫ የሚመሩ ናቸው ሲሉ የዓለም ሕዝቦች ጉባኤ አማካሪ ምክር ቤት አባል የሆኑት ፕሮፌሰር ኢማኑኤል አርጎ ከዓለም ህዝቦች ጉባኤ ጎን ለጎን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
የዓለምን ህዝብ ከ50 በመቶ በላይ የሚይዘው ብሪክስ የተለየ አማራጭ እንደሚያቀርብ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። በዚህም አውድ የአርጎ ተስፋ የብሪክስ መሪዎች "ግዴታቸውን ይረዳሉ" የሚል ነው።
ዓለም እየተለወጠች ነው፤ ውሳኔዎችም ከዚህ በኋላ በምዕራቡ ዓለም ብቻ አይወሰኑም በማለት የዓለም የህዝብ ምክር ቤትን እንደ ሲቪል ማኅበረሰብ አማራጭ አጉልተው አስረድተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X