የአትሌቲክስ ድልን ተከትሎ በቦትስዋና ሀገር አቀፍ የድል በዓል ቀን ታወጀ
20:25 22.09.2025 (የተሻሻለ: 20:34 22.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአትሌቲክስ ድልን ተከትሎ በቦትስዋና ሀገር አቀፍ የድል በዓል ቀን ታወጀ
በቶኪዮ በተካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ የወንዶች 4x400 (1600) ሜትር የዱላ ቅብብል ቡድን ላመጣው የወርቅ ሜዳሊያ ክብር ሴፕቴምበር 29ን የሕዝብ በዓል አድርጋ አውጃለች፡፡ ቦትስዋና ይህንን ውድድር ያሸነፈች የመጀመሪያዋ የአፍሪካ ሀገር ሆናለች።
ፕሬዝዳንት ዱማ ቦኮ ዝናብ እየዘነበ በተካሄደው የፍጻሜ ውድድር ቡድኑ የአሜሪካንን ቡድን በማሸነፉ ድሉን “ታሪካዊ የአፍሪካ ድል” ሲሉ አሞካሽተዋል፡፡ ደቡብ አፍሪካ በበኩሏ የውድድሩን የነሐስ ሜዳሊያ አግኝታለች።
አገሪቷ በውድድሩ በሁለት ወርቅ፣ በአንድ ብር እና በአንድ ነሐስ ሜዳሊያ እስካሁን ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በአጠቃላይ አምስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X