የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር አስተዳደርን ኢትዮጵያ ከተረከበች በኋላ ኩባንያው ትርፋማ መሆኑ ተገለፀ
18:21 22.09.2025 (የተሻሻለ: 18:34 22.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር አስተዳደርን ኢትዮጵያ ከተረከበች በኋላ ኩባንያው ትርፋማ መሆኑ ተገለፀ
የጭነት ባቡር መስመሩ ስራ ከጀመረበት እ.ኤ.አ. ከ2018 ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ትርፋማ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ፕሮጀክቱ ሥራ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ለስድስት ዓመታት ያስተዳደረው የቻይና የባቡር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ኃላፊነቱን በግንቦት 2024 ለኢትዮጵያ እና ለጅቡቲ ባለሥልጣናት በይፋ ማስረከቡ ይታወሳል።
የባቡር መስመሩን ትርፋማ እንዲሆን የተወሰዱ እርምጃዎች፦
ሥልጠና፣
ጠንካራ የአሰራር ቁጥጥር እና
የተሻለ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም
የኩባንያው ዓመታዊ የጭነት መጠን ወደ 6 ሚሊዮን ቶን አድጎ 90 በመቶ የሚሆነውን የኢትዮጵያ ምርት ወደ ጅቡቲ ወደብ ለሚያጓጉዘው የባቡር መስመር ከፍተኛ ገቢ አስገኝቷል።
የባቡር መስመሩ ትርፋማ ቢሆንም እንደ የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት እና የሎኮሞቲቭ ጥገና አስፈላጊነት ያሉ ችግሮች አሁንም ያጋጥሙታል ሲሉ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኙ ምስሎች
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

1/4
© telegram sputnik_ethiopia

2/4
© telegram sputnik_ethiopia

3/4
© telegram sputnik_ethiopia

4/4
© telegram sputnik_ethiopia
1/4
© telegram sputnik_ethiopia
2/4
© telegram sputnik_ethiopia
3/4
© telegram sputnik_ethiopia
4/4
© telegram sputnik_ethiopia