የደቡብ ሱዳን የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት በቀረበባቸው የሀገር ክህደት ክስ ችሎት ቀረቡ
16:46 22.09.2025 (የተሻሻለ: 16:54 22.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የደቡብ ሱዳን የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት በቀረበባቸው የሀገር ክህደት ክስ ችሎት ቀረቡ
የቀድሞ የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪክ ማቻር፣ የሱዳን ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ እንዲሁም ሰባት ሌሎች ግለሰቦችም ችሎት ቀርበዋል ሲሉ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ሁሉም ተጠርጣሪዎች የተከሰሱት፦
🟠 በሀገር ክህደት፣
🟠 በግድያ፣
🟠 በሴራ፣
🟠 የሽብርቶችን የሽብር እንቅስቃሴ በገንዘብ መርዳት፣
🟠 በመንግሥት ሥልጣን ላይ ወንጀል መፈፀም እና
🟠 ሰብአዊ ላይ በሚፈፀሙ ወንጀሎች ናቸው።
ክሱ የቀረበው በመጋቢት ወር በሰሜናዊ ደቡብ ሱዳን ውስጥ ከተቃዋሚው ጋር የተሰለፉ ታጣቂ ቡድኖች እና መደበኛ ጦር መካከል በተፈጠረ ግጭት ምክንያት ነው።
እንደ አንዳንድ ዘገባዎች ከሆነ በግጭቱ ከ250 በላይ ወታደሮች ተገድለዋል። በምርመራው ወቅት ማቻር በቁም እስር እንዲቆዩ ተደርጓል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X