የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በኮባልት ምርት ላይ የጣለችውን ገደብ በዓመታዊ ኮታ ልትተካ እንደሆነ አስታወቀች
19:43 21.09.2025 (የተሻሻለ: 19:44 21.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በኮባልት ምርት ላይ የጣለችውን ገደብ በዓመታዊ ኮታ ልትተካ እንደሆነ አስታወቀች
የስትራቴጂክ ማዕድን ሀብቶች ገበያ ደንብና ቁጥጥር ባለሥልጣን፤ ማዕድን አውጪዎች ከ2025 መጨረሻ እስከ 18 ሺህ 125 ቶን ኮባልት ወደ ውጭ መላክ እንደሚችሉ፤ በ2026 እና 2027 ደግሞ ኮታው 96 ሺህ 600 ቶን እንደሚደርስ አስታውቋል።
የአዲሱ ኮታ ሥርዓት ዓላማዎች፦
🟠 ክምችትን መቀነስ፤
🟠 ዋጋ ማረጋጋት፣
🟠 በምስራቅ ኮንጎ ለግጭት ምክንያት የሆነውን ሕገ-ወጥ የማዕድን ብዝበዛ መዋጋት።
በተጨማሪም ወደፊት ከሚላከው ምርት መጠን 10 በመቶ የሚሆነው ለሀገር አቀፍ ፕሮጀክቶች የሚቀመጥ ሲሆን ኮታው በገበያው ሁኔታ መሠረት ማስተካከያ ሊደረግበት ይችላል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X