የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የውሃ አካላትን መጠን እየጨመረ እንደሆነ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ
17:32 21.09.2025 (የተሻሻለ: 17:34 21.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የውሃ አካላትን መጠን እየጨመረ እንደሆነ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ
የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ባደረገው ጥናት፤ በስድስት ሀይቆች ማለትም በሐረማያ፣ በአቢያታ፣ በጣና፣ በዝዋይ፣ በጨለለቃ እና በአደሌ የውሃ መጠን ባለፉት 30 ዓመታት በእጅጉ መጨመሩን አረጋግጧል።
የተቀናጀ ውሃ ሃብት አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ደበበ ደፈርሶ ችግኝ ተከላው የአፈር መሸርሸርን ከመቀነሱም በላይ የውሃ ስርገት በማሻሻል የከርሰ ምድር ውሃ መጠን እንዲጨምር ማድረጉን ተናግረዋል።
ኢንስቲትዩቱ የአረንጓዴ አሻራን ይበልጥ ለመደገፍ በተጎዱ አካባቢዎች የችግኝ ተከላን ለመምራት የሚያስችል መረጃዎችንም ይሰበስባል።
የሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X