የሩሲያ ተዋጊ ጄቶች የኢስቶኒያን የአየር ክልል አልጣሱም ሲል የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስተባበለ
15:12 20.09.2025 (የተሻሻለ: 15:14 20.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ ተዋጊ ጄቶች የኢስቶኒያን የአየር ክልል አልጣሱም ሲል የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስተባበለ
ሦስት የሩሲያ ሚግ-31 ተዋጊ ጄቶች አርብ ከካሬሊያ ወደ ካሊኒንግራድ ክልል አየር ማረፊያ የታቀደ በረራ ማድረጋቸውን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ገልጿል።
በረራው የሌሎችን ሀገራት የአየር ክልል ሳይጥስ በዓለም አቀፍ የአየር ክልል ሕግ መሠረት በጥብቅ እንደተከናወነና ይህም በተጨባጭ መቆጣጠሪያዎች እንደተረጋገጠ ሚኒስቴሩ አስገንዝቧል።
አውሮፕላኑ መስመሩን እንዳልሳተ እና በኢስቶኒያ የአየር ክልል እንዳልገባም ተጠቅሷል። የውጊያ ጄቶቹ ከቫይንድሎ ደሴት 3 ኪሎ ሜትር በላይ በባልቲክ ባሕር ገለልተኛ ውሃ ላይ መብረራቸው ተገልጿል።
የኢስቶኒያ ዲፕሎማሲ የሩሲያ ሚግ-31 ተዋጊ ጄቶች የሀገሪቱን የአየር ክልል ጥሰዋል በሚል በታሊን የሞስኮን ተወካይ በመጥራት አቤቱታ አቅርቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X