የሩሲያ ተዋጊ ጄቶች የኢስቶኒያን የአየር ክልል አልጣሱም ሲል የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስተባበለ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየሩሲያ ተዋጊ ጄቶች የኢስቶኒያን የአየር ክልል አልጣሱም ሲል የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስተባበለ
የሩሲያ ተዋጊ ጄቶች የኢስቶኒያን የአየር ክልል አልጣሱም ሲል የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስተባበለ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 20.09.2025
ሰብስክራይብ

የሩሲያ ተዋጊ ጄቶች የኢስቶኒያን የአየር ክልል አልጣሱም ሲል የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስተባበለ

ሦስት የሩሲያ ሚግ-31 ተዋጊ ጄቶች አርብ ከካሬሊያ ወደ ካሊኒንግራድ ክልል አየር ማረፊያ የታቀደ በረራ ማድረጋቸውን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ገልጿል።

በረራው የሌሎችን ሀገራት የአየር ክልል ሳይጥስ በዓለም አቀፍ የአየር ክልል ሕግ መሠረት በጥብቅ እንደተከናወነና ይህም በተጨባጭ መቆጣጠሪያዎች እንደተረጋገጠ ሚኒስቴሩ አስገንዝቧል።

አውሮፕላኑ መስመሩን እንዳልሳተ እና በኢስቶኒያ የአየር ክልል እንዳልገባም ተጠቅሷል። የውጊያ ጄቶቹ ከቫይንድሎ ደሴት 3 ኪሎ ሜትር በላይ በባልቲክ ባሕር ገለልተኛ ውሃ ላይ መብረራቸው ተገልጿል።

የኢስቶኒያ ዲፕሎማሲ የሩሲያ ሚግ-31 ተዋጊ ጄቶች የሀገሪቱን የአየር ክልል ጥሰዋል በሚል በታሊን የሞስኮን ተወካይ በመጥራት አቤቱታ አቅርቧል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0