የዓለም ባንክ አፍሪካን ችላ በማለት ትኩረቱን በሙሉ ወደ ዩክሬን እንዳደረገ ተንታኙ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየዓለም ባንክ አፍሪካን ችላ በማለት ትኩረቱን በሙሉ ወደ ዩክሬን እንዳደረገ ተንታኙ ተናገሩ
የዓለም ባንክ አፍሪካን ችላ በማለት ትኩረቱን በሙሉ ወደ ዩክሬን እንዳደረገ ተንታኙ ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 20.09.2025
ሰብስክራይብ

የዓለም ባንክ አፍሪካን ችላ በማለት ትኩረቱን በሙሉ ወደ ዩክሬን እንዳደረገ ተንታኙ ተናገሩ

የዓለም ባንክ ከአፍሪካ ሀገራት ይልቅ ለዩክሬን ቅድሚያ መስጠቱ ባንኩ ወደ ምዕራባውያን ጂኦፖለቲካዊ ጥቅሞች ማዘንበሉን ያሳያል፤ ሲሉ በደቡብ አፍሪካ የፍሪ ስቴት ዩኒቨርሲቲ የድህረ ዶክትሬት ባልደረባ ታፋዝዋ ሩዚቭ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

የዓለም ባንክ ባለፉት ሶስት ዓመታት ከሁሉም የአፍሪካ ሀገራት ድምር በላይ ለዩክሬን ከፍተኛ ብድር መስጠቱ፤ የድህነት ቅነሳ እና ዘላቂ ልማት ግቦቹን ወደ ጎን እንዳለ ያሳያል ብለዋል።

"የዓለም ባንክ አጠቃላይ የዩክሬን ሀገርን ለዎል ስትሪት የገንዘብ አበዳሪዎቹ ጥቅም በዋስትና ለማስያዝ አፍሪካን ትቶ በዩክሬን ኢንቨስት እያደረገ ነው" ያሉት ዶ/ር ሩዚቭ፤ ብድሩ ለዩክሬን የሚፈሰው ከግጭቱ በኋላ የተፈጥሮ ሀብቶቿን እና የመንግሥት ንብረቶቿን ለመቆጣጠር ነው ሲሉም ሞግተዋል።

የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ለአፍሪካ ሀገራት ደንታ ቢስ መሆናቸውን በመተቸት፤ እነዚህ ተቋማት "የአፍሪካን መሠረታዊ ችግሮች ለመፍታት ተጨንቀውም ፈልገውም አያውቁም" ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0