የአውሮፓ ኅብረት ኮሚሽን በ19ኛው ዙር ማዕቀብ የታገዱ የሩሲያ ንብረቶችን ለዩክሬን ብድር በማስያዣነት ለመጠቀም ሀሳብ ማቅረቡን ኧርሰላ ቮን ደር ሌይን ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአውሮፓ ኅብረት ኮሚሽን በ19ኛው ዙር ማዕቀብ የታገዱ የሩሲያ ንብረቶችን ለዩክሬን ብድር በማስያዣነት ለመጠቀም ሀሳብ ማቅረቡን ኧርሰላ ቮን ደር ሌይን ተናገሩ
የአውሮፓ ኅብረት ኮሚሽን በ19ኛው ዙር ማዕቀብ የታገዱ የሩሲያ ንብረቶችን ለዩክሬን ብድር በማስያዣነት ለመጠቀም ሀሳብ ማቅረቡን ኧርሰላ ቮን ደር ሌይን ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.09.2025
ሰብስክራይብ

የአውሮፓ ኅብረት ኮሚሽን በ19ኛው ዙር ማዕቀብ የታገዱ የሩሲያ ንብረቶችን ለዩክሬን ብድር በማስያዣነት ለመጠቀም ሀሳብ ማቅረቡን ኧርሰላ ቮን ደር ሌይን ተናገሩ

እቅዱ ወደ አባል ሀገራቱ የሚገባውን ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ አቅርቦት እገዳንም እንደሚያካትት የኮሚሽኑ ፕሬዝዳንት አስታውቀዋል፡፡

የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ገንዘብ በአውሮፓ መታገዱን በተደጋጋሚ ስርቆት ነው ሲል አውግዟል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ሞስኮ በሩሲያ የምዕራባውያን ሀገራት ንብረቶችን በመከልከል ምላሽ ልትሰጥ ትችላለች ሲሉ አስጠንቅቀው ነበር።

እ.ኤ.አ በ2022 ሩሲያ በዩክሬን ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ ከጀመረች በኋላ የአውሮፓ ኅብረት እና የቡድን 7 ጥምረት በድምሩ 300 ቢሊዮን ዩሮ የሚገመተውንና ከሩሲያ የውጭ ምንዛሪ ክምችት ግማሽ ያህሉን አግደዋል።

የአውሮፓ ኅብረት የሩሲያን ንብረቶች ለመስረቅ የሚያደርገው ሙከራ በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓት ላይ የከፋ አሉታዊ መዘዝ ይዞ እንደሚመጣ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ በመስከረም ወር መጀመሪያ ላይ ተናግረዋል።

በእንግሊዝኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0