ቡርኪና ፋሶ በ2024 በአፍሪካ የወርቅ ማዕድን ዘርፍ ቦታዋን አስጠብቃለች
20:09 17.09.2025 (የተሻሻለ: 20:14 17.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ቡርኪና ፋሶ በ2024 በአፍሪካ የወርቅ ማዕድን ዘርፍ ቦታዋን አስጠብቃለች
የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር በ2024 ወደ 60.8 ቶን የሚጠጋ ወርቅ ማምረት ችላለች፡፡ በዚህም በ2023 ከተገኘው 56.8 ቶን እና በ2022 ከተገኘው 57.6 ቶን ብልጫ ያለው ሲሆን የሚልቀውን መጠን ለወጪ ንግድ መቅረቡን የማዕድን ሚኒስቴር ዋና ፀሐፊ ዱላዬ ሳኑ ተናግረዋል።
በቁጥር ሲቀመጥ፡-
▪ከ2008 ጀምሮ እድገት አሳይቷል (5.6 ቶን)፤ ከ10 እጥፍ በላይ ጭማሪ።
▪ወጪ ንግድ፡ በ2024 ከጠቅላላ የወጪ ንግድ ዋጋ 84 በመቶ ይይዛል ፤ (በ2023 ከነበረው 80.4 በመቶ የ3.6 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል)።
ኢኮኖሚያዊ ተፅእኖ፡-
▪የመንግሥት ቀጥታ ገቢ፡ በ2024 ወደ 1.02 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል።
▪የማዕድን ኢንዱስትሪው አስተዋጽኦ የሀገር ውስጥ ልማትን ይደግፋል።
የማዕድን ዘርፍ መልክ
▪22 የኢንዱስትሪ ማዕድን ፍቃዶች ተሰጥተዋ፤ በአሁኑ ጊዜ 13 ማዕድን አውጪዎች በማምረት ላይ ይገኛሉ።
▪ከፍተኛ የኤክስፖርት ገበያዎች፡ የተባበሩት የአረብ ኤምሬቶች እና ስዊዘርላንድ ከጠቅላላ የወጪ ንግድ 89.2 በመቶውን ይይዛሉ።
ብሔራዊ ፖሊሲ
▪ብሔራዊ የውድ ንጥረ ነገሮች ማኅበር ለሀገር አቀፍ ክምችት ግንባታ 13.049 ቶን ወርቅ ገዝቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X