ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከሕንዱ ጥቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የስልክ ንግግር አደረጉ
16:05 17.09.2025 (የተሻሻለ: 16:14 17.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከሕንዱ ጥቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የስልክ ንግግር አደረጉ
ዛሬ ማለዳ ፑቲን 75ኛ ዓመት የልደት በዓላቸው ለሚያከብሩት ሞዲ ሞቅ ያለ ሰላምታ አቅርበዋል፡፡
የሩሲያው ፕሬዝዳንት "በአገሮቻችን መካከል ያለውን ልዩ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማጠናከር እና በተለያዩ ዘርፎች የጋራ ተጠቃሚነት ያለውን የሩሲያ እና ሕንድ ትብብር ለማሳደግ በግልዎ ትልቅ አበርክቶ እያደረጉ ነው" ሲሉ በእንኳን አደረሰዎት መልእክታቸው ገለፀዋል፡፡
ሕንድ በሞዲ አመራር ስር በማሕበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ሳይንሳዊ እና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ሁሉ ያስመዘገበቻቸውን "አስደናቂ ስኬቶች" አሞካሽተዋል፡፡ እንዲሁም በሁለትዮሽ፣ በቀጣናዊ እና በዓለም አቀፍ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ ትብብርን ለማጠናከር የሩሲያን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
ፑቲን የስልክ ንግግር ከማድረጋቸው አስቀድሞ ዛሬ ጠዋት ለሞዲ "መልካም ጤንነት፣ ደስታ፣ ብልጽግና እና አዳዲስ ስኬቶች" ተመኝተውላቸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X