https://amh.sputniknews.africa/20250917/1601890.html
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከሕንዱ ጥቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የስልክ ንግግር አደረጉ
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከሕንዱ ጥቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የስልክ ንግግር አደረጉ
Sputnik አፍሪካ
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከሕንዱ ጥቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የስልክ ንግግር አደረጉ ዛሬ ማለዳ ፑቲን 75ኛ ዓመት የልደት በዓላቸው ለሚያከብሩት ሞዲ ሞቅ ያለ ሰላምታ አቅርበዋል፡፡ የሩሲያው ፕሬዝዳንት "በአገሮቻችን መካከል ያለውን ልዩ... 17.09.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-09-17T16:05+0300
2025-09-17T16:05+0300
2025-09-17T16:14+0300
sputnik africa
telegram sputnik_ethiopia
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/img/07e9/09/11/1601736_0:0:680:383_1920x0_80_0_0_b90839a722df4409fd8e02db6d4d48be.jpg
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከሕንዱ ጥቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የስልክ ንግግር አደረጉ ዛሬ ማለዳ ፑቲን 75ኛ ዓመት የልደት በዓላቸው ለሚያከብሩት ሞዲ ሞቅ ያለ ሰላምታ አቅርበዋል፡፡ የሩሲያው ፕሬዝዳንት "በአገሮቻችን መካከል ያለውን ልዩ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማጠናከር እና በተለያዩ ዘርፎች የጋራ ተጠቃሚነት ያለውን የሩሲያ እና ሕንድ ትብብር ለማሳደግ በግልዎ ትልቅ አበርክቶ እያደረጉ ነው" ሲሉ በእንኳን አደረሰዎት መልእክታቸው ገለፀዋል፡፡ ሕንድ በሞዲ አመራር ስር በማሕበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ሳይንሳዊ እና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ሁሉ ያስመዘገበቻቸውን "አስደናቂ ስኬቶች" አሞካሽተዋል፡፡ እንዲሁም በሁለትዮሽ፣ በቀጣናዊ እና በዓለም አቀፍ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ ትብብርን ለማጠናከር የሩሲያን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።ፑቲን የስልክ ንግግር ከማድረጋቸው አስቀድሞ ዛሬ ጠዋት ለሞዲ "መልካም ጤንነት፣ ደስታ፣ ብልጽግና እና አዳዲስ ስኬቶች" ተመኝተውላቸዋል።በእንግሊዝኛ ያንብቡ ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
2025
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/img/07e9/09/11/1601736_85:0:596:383_1920x0_80_0_0_7916a0fc49b87c552d6e2fc432bf652d.jpgSputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
sputnik africa, telegram sputnik_ethiopia
sputnik africa, telegram sputnik_ethiopia
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከሕንዱ ጥቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የስልክ ንግግር አደረጉ
16:05 17.09.2025 (የተሻሻለ: 16:14 17.09.2025) ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከሕንዱ ጥቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የስልክ ንግግር አደረጉ
ዛሬ ማለዳ ፑቲን 75ኛ ዓመት የልደት በዓላቸው ለሚያከብሩት ሞዲ ሞቅ ያለ ሰላምታ አቅርበዋል፡፡
የሩሲያው ፕሬዝዳንት "በአገሮቻችን መካከል ያለውን ልዩ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማጠናከር እና በተለያዩ ዘርፎች የጋራ ተጠቃሚነት ያለውን የሩሲያ እና ሕንድ ትብብር ለማሳደግ በግልዎ ትልቅ አበርክቶ እያደረጉ ነው" ሲሉ በእንኳን አደረሰዎት መልእክታቸው ገለፀዋል፡፡
ሕንድ በሞዲ አመራር ስር በማሕበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ሳይንሳዊ እና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ሁሉ ያስመዘገበቻቸውን "አስደናቂ ስኬቶች" አሞካሽተዋል፡፡ እንዲሁም በሁለትዮሽ፣ በቀጣናዊ እና በዓለም አቀፍ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ ትብብርን ለማጠናከር የሩሲያን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
ፑቲን የስልክ ንግግር ከማድረጋቸው አስቀድሞ ዛሬ ጠዋት ለሞዲ "መልካም ጤንነት፣ ደስታ፣ ብልጽግና እና አዳዲስ ስኬቶች" ተመኝተውላቸዋል።
በእንግሊዝኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X