ሶማሊያ የኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ እንደምትደግፍ አስታወቀች
14:15 17.09.2025 (የተሻሻለ: 11:34 18.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሶማሊያ የኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ እንደምትደግፍ አስታወቀች
የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ በሰላማዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ የኢትዮጵያን የባሕር በር የመፈለግ መብት እንደሚደገፉ መናገራቸውን ከአል አረቢያ ቲቪ ጋር ያደረጉትን ቃለ ምልልስ ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡
"የኢትዮጵያ የባሕር በር ፍላጎት በዓለም አቀፍ ሕግ ማዕቀፍ ውስጥ አዲስ አይደለም፤ ማንኛውም ሀገር ዓለም አቀፍ ሕግጋት እና አኅጉራዊ ስምምነቶችን እስካከበረ ድረስ ጥቅሙን ለማስጠበቅ ሊጠቀምባቸው የሚችላቸው እውቅና ያላቸው ዘዴዎች እና አካሄዶች አሉ" ብለዋል።
ኢትዮጵያ ሕጋዊ መንገዶችን ከተከተለች ማሳካት እንደምትችልና ድጋፋቸውን እንደሚሰጡም ተናግረዋል፡፡
"በቀይ ባሕር አዋሳኝ አገሮች፣ የጸጥታና የኢኮኖሚ ፍላጎት ያላቸው አገሮች መረጋጋትን በሚያመጡና ሁሉንም የሚያገለግሉ የጋራ መግባባቶች እንዲፈጠሩ በውይይት፣ በመግባባትና ትብብር ላይ ሲሰሩ ይገባል፡፡" ሲሉ አሳስበዋል፡፡
ፕሬዝዳንቱ አክለውም የሶማሊያ አቋም ጽኑ እና ግልጽ ነው ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X