የኬንያው ኢኩዊቲ ባንክ የኢትዮጵያን የባንክ ዘርፍ ለመቀላቀል ከኢትዮጵያ ባለሥልጣን ጋር እየተነጋገረ ነው
21:08 16.09.2025 (የተሻሻለ: 21:14 16.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኬንያው ኢኩዊቲ ባንክ የኢትዮጵያን የባንክ ዘርፍ ለመቀላቀል ከኢትዮጵያ ባለሥልጣን ጋር እየተነጋገረ ነው
የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጀምስ ምዋንጊ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን ጋር ገበያውን በሚቀላቀሉበት ወሳኝ ሂደቶች ላይ አርብ ዕለት መነጋገራቸውን የኬንያ ሚዲያ ዘግቧል፡፡
ጀምስ ምዋንጊ፣ የውጭ ኢንቨስተሮች በፋይናንስ ዘርፉ እንዲቀላቀሉ መንግስት ያሳለፈው ውሳኔ ምቹ ሁኔታን እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡
ኮሚሽነር ተመስገን ባንኩ ወደ ሀገሪቱ የፋይናንስ ዘረፍ የሚቀላቀልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት አስፈላጊውን ድጋፍ እና ትብብር ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
ዋና መቀመጫውን ናይሮቢ ያደረገው ኢኩዊቲ ባንክ ኬንያን ጨምሮ በዲሞክራቲክ ኮንጎ፣ ኡጋንዳ፣ ሩዋንዳ ደቡብ ሱዳንና ታንዛኒያ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
ባንኩ ከኢትዮጵያ ባንኮች የ40 በመቶ ድርሻን ለመግዛት ሀሳብ ማቅረቡ እና ከብሔራዊ ባንክ ጋር ንግግር ላይ መሆናቸውን ፖል ሩሶ አስታውቀዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia