ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የስፖርት ትብብራቸውን ለማሳደግ ተስማሙ
14:10 16.09.2025  (የተሻሻለ: 14:24 16.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
 / ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የስፖርት ትብብራቸውን ለማሳደግ ተስማሙ
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በቀጣይ ወራት በሚካሄዱ የሳማራ እና ሞስኮ ማራቶኖች ላይ እንዲሳተፉ ሩስያ ጥሪ አቅርባለች፡፡
የሩስያ ስፖርት ሚኒስትር ድያግተረቭ ቭላድሚሮቪች ከኢትዮጵያ ባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማህዲ ጋር በነበራቸው ቆይታ ጥሪውን ያቀረቡ ሲሆን ሁለቱ ሀገራት በዘርፉ በትብብር ሊሰሩባቸው በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ተነጋግረዋል፡፡
ሚኒስተር ዴኤታዋ በበኩላቸው በአትሌቲክስ ብሎም በእግር ኳሱ የወዳጅነት ጨዋታዎችን በማዘጋጀት በዘርፉ በትብብር ሊሰሩባቸው የሚችሉባቸውን ዘርፎች ጠቁመዋል፡፡
ድያግተረቭ አክለውም በስፖርት ዘርፍ ማጥናት የሚፈልጉ ተማሪዎችን በ14 የሩስያ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ማስተማርና የመቀበል ምጣኔውን ለማሳደግ ዝግጁነታቸውን ገልፀዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

