ኢትዮጵያ የአፍሪካን የአየር ጉዞን ዳግም የሚበይነውን የቢሾፍቱ ኤርፖርት ፕሮጀክት አስጀመረች
13:25 16.09.2025  (የተሻሻለ: 13:54 16.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
 / ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የአፍሪካን የአየር ጉዞን ዳግም የሚበይነውን የቢሾፍቱ ኤርፖርት ፕሮጀክት አስጀመረች
የኤርፖርቱ ግንባታ በዓመት እስከ 100 ሚሊዮን ተጓዦችን ለማስተናገድ እንዲችል
የታቀደ ሲሆን ይህም ከአፍሪካ ግዙፉ ያደርገዋል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፤ ነባሩ የቦሌ ኤርፖርት ከ10 እስከ 15 በመቶ በደረሰ የእድገት ምጣኔ ባለፈው ዓመት 20 ሚሊዮን ያህል ተጓዦችን ማስተናገዱን ገልፀው አዲሱ ኤርፖርት ትስስርን ለማሳደግ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ 145 መዳረሻዎችን ለማገናኘት እንደሚያግዝ ጠቁመዋል፡፡
ባለፉተ ሁለት ዓመታት የግንባታ ስፍራውን የማዘጋጀት፣ የአካባቢው ነዋሪ ዜጎችን ወደ ሌላ ስፍራ የማዘወርና የአስተዳደር መዋቅር ሲሠራ ቆይቷል፡፡
የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ፣ ፕሮጀክቱ አካባቢያዊ ጥበቃን ዘላቂ ለማድረግ የሚኖረውን ሚና በማንሳት በንግድ፣ በቱሪዝም እና ስራ ፈጠራ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እንደሚያግዘው አስረድተዋል፡፡
በዳር አልሃንዳሽ ኩባንያ የቴክኒካል ድጋፍ እና በአፍሪካ ልማት ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የሚገነባው ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያን እና የአፍሪካን የአቪዬሽን ምሕዳር ወደ ላቀ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው ታምኖበታል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X



