ሩሲያ በኢንተርቪዥን ውድድር እንግዳ ተቀባይነቷን እና ፍትሐዊ ውድድርን ታሳያለች - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር
13:05 16.09.2025  (የተሻሻለ: 13:14 16.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
 / ሰብስክራይብ
ሩሲያ በኢንተርቪዥን ውድድር እንግዳ ተቀባይነቷን እና ፍትሐዊ ውድድርን ታሳያለች - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር
“ውድድሩ ፍትሐዊ ይሆናል፤ ብርቱ የሆነው ደግሞ ያሸንፋል፡፡” ሲሉ ዲሚትሪ ቼርኒሼንኮ ለኮንፍረንሱ ታዳሚያን ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡
የመጪው ኢንተርቪዥን የሙዚቃ ውድድር አዘጋጅ ኮሚቴ ሊቀመንበር የሆኑት ቼርኒሼንኮ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ለውድድሩ የሚደረገውን ዝግጅት ለሚያደርጉት የግል ክትትል የአክብሮት ምስጋናቸውን ገልፀውላቸዋል፡፡
ከወጣቶች ፌስቲቫል የተውጣጡ ከ100 በላይ ተሳታፊዎች በዋናነት በጎዳና የቡድን ትራኢት (ፍላሽ ሞብ) ለመሳተፍ ኢንተርቪዥንን ውድድር ላይ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልፀዋል።
የውድድሩ በጎ ፈቃደኞች ከአራት ወዳጅ ሀገራት ማለትም ከቬትናም፣ ኡዝቤኪስታን፣ ታጂኪስታን እና ቤላሩስ የመጡ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X