የአፍሪካ ስታርትአፖች በ2025 ከ2 ቢሊየን ዶላር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ማግኘታቸውን ሪፖርቶች አለመላከቱ
20:13 15.09.2025 (የተሻሻለ: 20:14 15.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአፍሪካ ስታርትአፖች በ2025 ከ2 ቢሊየን ዶላር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ማግኘታቸውን ሪፖርቶች አለመላከቱ
ብሪተር ብሪጅስ የተባለ ድርጅት ባወጣው ሪፖርት መሠረት፤ በአኅጉሪቱ የሚገኙ የንግድ ተቋማት በመጀመሪያዎቹ ስምንት ወራት ውስጥ 2 ነጥብ 8 ቢሊየን ዶላር አሰባስበዋል፡፡ ይህም እ.ኤ.አ. በ2024 ከተገኘው አጠቃላይ የገንዘብ መጠን ጋር ተመሳሳይ ነው።
በሪፖርቱ ውስጥ ከተጠቀሱት ዋና ዋና ነጥቦች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦
ምስራቅ አፍሪካ በገንዘብ ድጋፍ መጠን ቀዳሚ ስፍራን በመያዝ 865 ሚሊየን ዶላር ሲያስመዘግብ ደቡባዊ አፍሪካ ደግሞ 845 ሚሊየን ዶላር አግኝቷል።
ለመጀመሪያ ጊዜ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ያላቸው ንግዶችን የሚደግፈዉ የዕዳ ፋይናንስ 1 ቢሊየን ዶላር ደርሷል።
ቴክኖሎጂ መር የገንዘብ ዘርፍ አሁንም ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኝ ቢሆንም፣ የንጹህ ቴክኖሎጂ ኃይል ዘርፍ እያደገ በመምጣት 1 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አሰባስቧል።
ዘርፉ እ.ኤ.አ. በ2022 ካጋጠመው የገንዘብ ድጋፍ እጥረት እያገገመ ሲሆን ከሁለት ዓመታት ውድቀት በኋላ 2025 የማገገሚያ ዓመት ተብሎ ተመድቧል።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X