ለ2018 የትምህርት ዘመን የተመዘገቡ ተማሪዎች ቁጥር ወደ 22 ሚሊዮን ከፍ ማለቱን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ
17:11 15.09.2025  (የተሻሻለ: 17:14 15.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
 / ሰብስክራይብ
ለ2018 የትምህርት ዘመን የተመዘገቡ ተማሪዎች ቁጥር ወደ 22 ሚሊዮን ከፍ ማለቱን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እሰከ ትናንትናው ዕለት ድረስ የተመዘገቡት ተማሪዎች ቁጥር 22 ሚሊዮን 479 ሺህ 299 የደረሰ ሲሆን ይህም ቁጥር ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተመዘገቡት 15.3 ሚሊዮን ተማሪዎች ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል ብለዋል።
ሚኒስትሩ ለውጡ የመጣው ከዚህ ቀደም ግጭትን ጨምሮ በተለያዩ ምክንያቶች በተፈጠረው መስተጓጎል ምክንያት ትምህርታቸውን አቋርጠው የነበሩ ሕጻናት ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱ በጋራ የተደረገው ጥረት ውጤት እንደሆነ አመላክተዋል።
ምዝገባው አሁንም እንደቀጠለ በመሆኑ፤ የመጨረሻው የተማሪዎች ቁጥር በቀጣይ ቀናት የበለጠ ከፍ ሊል እንደሚችል ማስረዳታቸውን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X