ለ2018 የትምህርት ዘመን የተመዘገቡ ተማሪዎች ቁጥር ወደ 22 ሚሊዮን ከፍ ማለቱን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱለ2018 የትምህርት ዘመን የተመዘገቡ ተማሪዎች ቁጥር ወደ 22 ሚሊዮን ከፍ ማለቱን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ
ለ2018 የትምህርት ዘመን የተመዘገቡ ተማሪዎች ቁጥር ወደ 22 ሚሊዮን ከፍ ማለቱን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 15.09.2025
ሰብስክራይብ

ለ2018 የትምህርት ዘመን የተመዘገቡ ተማሪዎች ቁጥር ወደ 22 ሚሊዮን ከፍ ማለቱን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እሰከ ትናንትናው ዕለት ድረስ የተመዘገቡት ተማሪዎች ቁጥር 22 ሚሊዮን 479 ሺህ 299 የደረሰ ሲሆን ይህም ቁጥር ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተመዘገቡት 15.3 ሚሊዮን ተማሪዎች ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል ብለዋል።

ሚኒስትሩ ለውጡ የመጣው ከዚህ ቀደም ግጭትን ጨምሮ በተለያዩ ምክንያቶች በተፈጠረው መስተጓጎል ምክንያት ትምህርታቸውን አቋርጠው የነበሩ ሕጻናት ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱ በጋራ የተደረገው ጥረት ውጤት እንደሆነ አመላክተዋል።

ምዝገባው አሁንም እንደቀጠለ በመሆኑ፤ የመጨረሻው የተማሪዎች ቁጥር በቀጣይ ቀናት የበለጠ ከፍ ሊል እንደሚችል ማስረዳታቸውን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0