በሞስኮ የኢትዮጵያ ባሕሎች የደመቁበት የፊልሃርመኒክ አዳራሽ ድግስ
16:42 15.09.2025  (የተሻሻለ: 16:44 15.09.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
 / ሰብስክራይብ
በሞስኮ የኢትዮጵያ ባሕሎች የደመቁበት የፊልሃርመኒክ አዳራሽ ድግስ
በኢትዮጵያ የባሕልና ስፖርት ሚኒስቴር አዘጋጅነትና በሻኩራ ፕሮዳክሽን አስተባባሪነት ወደ ሞስኮ ያቀናው ኪን-ኢትዮጵያ ቡድን በሩስያ ሁለተኛ መድረኩን በልዩ ድምቀት ተካሂዷል።
በመድረኩ የኢትዮጵያን ቱባ ባሕል የሚያሳዩ ባሕላዊ ሙዚቃ፣ ውዝዋዜ፣ የባሕል አልባሳት ትዕይንተ-ፋሽን እንዲሁም የሰርከስ ትርዒት ቀርቧል።
ዝግጅቱን ሩሲያውያን፣ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት፣ ኢትዮጵያውያን እና በሩሲያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ታድመውታል፡፡
የመድረክ ሥራዎቹ ከመቅረባቸው አስቀድሞ ተሳታፊዎች የኢትዮጵያን ቡና እንዲያጣጥሙ ተድርጓል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X