አውሮፓ 'ለሰርቢያ ሜይዳን' እየተዘጋጀች ነው ሲል የሩሲያ የውጭ መረጃ አገልግሎት አስጠነቀቀ
14:37 15.09.2025 (የተሻሻለ: 15:04 15.09.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱአውሮፓ 'ለሰርቢያ ሜይዳን' እየተዘጋጀች ነው ሲል የሩሲያ የውጭ መረጃ አገልግሎት አስጠነቀቀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አውሮፓ 'ለሰርቢያ ሜይዳን' እየተዘጋጀች ነው ሲል የሩሲያ የውጭ መረጃ አገልግሎት አስጠነቀቀ
የሩሲያ የደህንነት አገልግሎት እንዳስታወቀዉ፤ የአውሮፓ ልሂቃን በኖቪ ሳድ (26 ሰዎች የሞቱበት የባቡር አደጋ) ጥቅምት 22 ታስቦ በሚውለው አሳዛኝ ክስተት ዓመታዊ ማስታወሻ ላይ ተቃውሞዎችን በማቀጣጠል ሁኔታውን ወደራሳቸው ለማዘንበል እያሰቡ ነው።
ትኩረቱ የሰርቢያ ወጣቶችን "አስተሳሰባቸውን ለማሳሳት" እና "ብሩህ የአውሮፓ የወደፊት" ተብሎ የሚጠራውን እቅድ ማስተዋወቅ ላይ ነው።
ብራስልስ የተቃውሞ ሰልፎችን ለማነሳሳት፤ መራጮችን ለማሰባሰብ እና "የሰርቢያ ሜይዳን" (በምዕራባውያን የሚደገፍ ከፍተኛ ተቃውሞ) ወደ ሕይወት ለማምጣት በሚዲያዎችን እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን የገንዘብ ድጋፍን ይተማመናል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X