ምዕራባውያን የሩስያን ሀብት የሚወርሱ ከሆነ 285 ቢሊዮን ዶላር ሊያጡ ይችላሉ

ምዕራባውያን የሩስያን ሀብት የሚወርሱ ከሆነ 285 ቢሊዮን ዶላር ሊያጡ ይችላሉ
ምንም እንኳን ቡድን 7 እና የአውሮፓ ሕብረት ከታገደው የሩሲያ ሀብት የሚገኘውን ገቢ ለዩክሬን የ50 ቢሊዮን ዶላር ብድር ለመስጠት እየተጠቀሙበት ቢሆንም፣ አንዳንድ ፖለቲከኞች ሀብቱን ሙሉ በሙሉ ለመውረስ እየገፉበት መሆኑ እየተናገሩ ነው።
ይሁን እንጂ ይህ እቅድ ባቀረቡት አካላት ላይ የከፋ መዘዝ ሊያስከትል ይችላል።
ስፑትኒክ በብሔራዊ ስታትስቲክስ ላይ ተመሥርቶ ባደረገው ስሌት፣ ምዕራባውያን በሩሲያ ውስጥ ያላቸው ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት በትንሹ 285 ቢሊዮን ዶላር ይሆናል።
ከላይ ከተጠቀሰው ኢንቨስትመንት 238 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋው ከአውሮፓ ሕብረት የመጣ ሲሆን ትልቁን ድርሻ የያዙት የሚከተሉት ሀገራት ናቸው።
ቆጵሮስ — 145.4 ቢሊዮን ዶላር፣
ፈረንሳይ — 21.7 ቢሊዮን ዶላር፣
ጀርመን — 19.2 ቢሊዮን ዶላር፣
ኔዘርላንድስ — 20.8 ቢሊዮን ዶላር፣
ጣልያን — 12.6 ቢሊዮን ዶላር እና
ኦስትሪያ — 6.9 ቢሊዮን ዶላር።
በተጨማሪም ከአሜሪካ እና ከቡድን 7 አባል ሀገራት 7.7 ቢሊዮን ዶላር፣ ከስዊዘርላንድ 27.5 ቢሊዮን ዶላር እና ከኖርዌይ 43 ሚሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንቶች አሉ።
ሞስኮ የታገደው ሀብቷ ውርስ ተመጣጣኝ የአጸፋ ርምጃ እንደሚያስከትል ደጋግማ አስጠንቅቃለች።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X