የእንግሊዝ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር የለንደን ተቃውሞዎች ወደ ብጥብጥ መቀየራቸውን ተከትሎ ክስ እንደሚመሠረት አስጠነቀቁ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየእንግሊዝ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር የለንደን ተቃውሞዎች ወደ ብጥብጥ መቀየራቸውን ተከትሎ ክስ እንደሚመሠረት አስጠነቀቁ
የእንግሊዝ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር የለንደን ተቃውሞዎች ወደ ብጥብጥ መቀየራቸውን ተከትሎ ክስ እንደሚመሠረት አስጠነቀቁ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 14.09.2025
ሰብስክራይብ

የእንግሊዝ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር የለንደን ተቃውሞዎች ወደ ብጥብጥ መቀየራቸውን ተከትሎ ክስ እንደሚመሠረት አስጠነቀቁ

በለንደን በተደረገው መጠነ ሰፊ ተቃውሞ ወቅት በፖሊስ ላይ ጥቃት በመሰንዘር የተሳተፈ የትኛውም ሰው ክስ ሊመሰረትበት እንደሚችል ሚኒስትሯ ሻባና ማሕሙድ አስጠንቅቀዋል፡፡

“በፖሊስ መኮንኖች ላይ ጥቃት የሰነዘሩትን እና ጉዳት ያደረሱትን አወግዛለሁ። በወንጀል ድርጊቱ ላይ ድርሻ ያለው የተኛውም ሰው የሕግን ሙሉ ኃይል ይጋፈጣል።” ሲሉ ማሕሙድ በኤክስ ገጻቸው ላይ ጽፈዋል።

ቅዳሜ ዕለት፣ ሰልፈኞቹ የቅዱስ ጊዮርጊስ መስቀልን እና የ’ዩኒየን ጃክ’ ባንዲራዎችን እያውለበለቡ ወደ ዋይትሆል ከማምራታቸው በፊት በ’ረስል ስኩዌር’ ተሰባስበዋል፡፡

ቶሚ ሮቢንሰን የመራው “ዩናይት ዘ ኪንግደም” ሰልፍ ተሳታፊዎች፣ የመንግሥትን የኢሚግሬሽን ፖሊሲዎች እና የመናገር ነጻነት ገደብ አድርገው የሚመለከቷቸውን ነገሮች አውግዘዋል፡፡ ፖሊስ የእርግጫ እና የቡጥ ድብደባዎችን አስተናግዷል፡፡

ፖሊስ በኤክስ ገጹ ላይ እንዳስታወቀው “ጠርሙሶች፣ ርችቶች እና ሌሎች ተወርዋሪ ነገሮች ተወርውረዋል”፤ እስካሁን ዘጠኝ ሰዎች መታሰራቸው የተረጋገጠ ሲሆን ሌሎች ብዙዎች ሊታሰሩ ይችላሉ።

በእንግሊዘኛ ለማንበብ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0