ጋቦን ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት በብቸኝነት በዜጎቿ እንዲመሩ ውሳኔ ልታሳልፍ ነው

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱጋቦን ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት በብቸኝነት በዜጎቿ እንዲመሩ ውሳኔ ልታሳልፍ ነው
ጋቦን ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት በብቸኝነት በዜጎቿ እንዲመሩ ውሳኔ ልታሳልፍ ነው - Sputnik አፍሪካ, 1920, 11.09.2025
ሰብስክራይብ

ጋቦን ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት በብቸኝነት በዜጎቿ እንዲመሩ ውሳኔ ልታሳልፍ ነው

ውሳኔው ተግባራዊ ሲሆን የውጭ ሀገር ዜጎች የፋይናንስ ተቋማትን እንዲመሩ የሚፈቀድላቸው በብሔራዊ ኢኮኖሚ እና ፋይናንስ ኮሚቴ ልዩ ፈቃድ ሲያገኙ ብቻ ነው ሲል የሚኒስትሮች ምክር ቤት በመግለጫው አስታውቋል።

ይህ እርምጃ በአመራር ቦታ ላይ ያለውን የውጭ ዜጎች የበላይነት በመግታት ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነትን ለማጠናከር ያለመ ነው ተብሏል።

እንደ ሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘገባ መንግሥት፦

🟠 በሀገር አቀፍ ደረጃ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ጉዳዮች ጋር የተጣጣመ አስተዳደርን ለማበረታታት፣

🟠 በባንክ ዘርፍ ላይ ያለውን እምነት ለመመለስ፣

🟠 የብድር አቅርቦት ተግዳሮቶችን ለመፍታት ውጥን አስቀምጧል።

በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል

በእንግሊዝኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0