ጋቦን ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት በብቸኝነት በዜጎቿ እንዲመሩ ውሳኔ ልታሳልፍ ነው
18:53 11.09.2025 (የተሻሻለ: 18:54 11.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ጋቦን ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት በብቸኝነት በዜጎቿ እንዲመሩ ውሳኔ ልታሳልፍ ነው
ውሳኔው ተግባራዊ ሲሆን የውጭ ሀገር ዜጎች የፋይናንስ ተቋማትን እንዲመሩ የሚፈቀድላቸው በብሔራዊ ኢኮኖሚ እና ፋይናንስ ኮሚቴ ልዩ ፈቃድ ሲያገኙ ብቻ ነው ሲል የሚኒስትሮች ምክር ቤት በመግለጫው አስታውቋል።
ይህ እርምጃ በአመራር ቦታ ላይ ያለውን የውጭ ዜጎች የበላይነት በመግታት ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነትን ለማጠናከር ያለመ ነው ተብሏል።
እንደ ሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘገባ መንግሥት፦
🟠 በሀገር አቀፍ ደረጃ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ጉዳዮች ጋር የተጣጣመ አስተዳደርን ለማበረታታት፣
🟠 በባንክ ዘርፍ ላይ ያለውን እምነት ለመመለስ፣
🟠 የብድር አቅርቦት ተግዳሮቶችን ለመፍታት ውጥን አስቀምጧል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X