ኢትዮጵያ እና ዚምባብዌ በቆሻሻ አስተዳደር ዙሪያ ትብብሮችን ቃኙ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ እና ዚምባብዌ በቆሻሻ አስተዳደር ዙሪያ ትብብሮችን ቃኙ
የዚምባብዌ ጂኦ ፖሞና የቆሻሻ አስተዳደር ኩባንያ ቀጣናዊ ትበብርን ዓላማው ያደረገ ጉብኝት በኢትዮጵያ አካሂዷል።
በኩባንያው ሥራ አስፈፃሚ የተመራው ልዑክ በዚህ ሳምንት በኢትዮጵያ ዋና ዋና የቆሻሻ አያያዝ ማሳያ ተቋማትን ተዘዋውሮ ተመልክቷል።
በታዳሽ ኃይል እና በድጋሚ ለአገልግሎት ማዋል የትብብር መስኮች እንዲሁም ከቆሻሻ ወደ ኃይል ሞዴሎችን ከተለያዩ የአፍሪካ ሁኔታዎች ጋር ማላመድ ላይ ያተኮረ ነበር።
ጉብኝቱ ከአየር ንብረት ጉባኤ ጎን ለጎን መካሄዱ በአህጉሪቱ የቆሻሻ አስተዳደር፤ የአረንጓዴ ፈጠራን ለማፋጠን የሚያስችሉ ትብብሮችን ለማጠናከር እድል እንደፈጠረ ጂኦ ፖሞና ጠቁሟል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X