- Sputnik አፍሪካ, 1920
Sovereignty Sources
ዓለም በሉላዊነት ምክንያት ስትተሳሰር ፤ ፕሮግራሙም አፍሪካ ባላት እምቅ የተፈጥሮ ኃብት፣ በማደግ ላይ ባለው የሕዝብ ቁጥሯ ፣ በወጣት ኃይሏ እና በአህጉሪቱ ባሉ አዳዲስ ግኝቶችና የመፍትሄ ሃሳቦች ያላትን የመወዳደር አቅምና ጥቅም በሰፊው ይዳስሳል፡፡ እንኳን ወደ 'ሶቨርኒቲ ሶርስ' ፕሮግራም በደህና መጡ፣

ያለምንም የውጭ እርዳታ እና ገደብ ፦ ኢትዮጵያን በውስጣዊ አቅሟ መተማመንን ያረጋገጠችበት ግድብ

ያለምንም የውጭ እርዳታ እና ገደብ ፦ ኢትዮጵያን በውስጣዊ አቅሟ መተማመንን ያረጋገጠችበት ግድብ
ሰብስክራይብ

''የህዳሴ ግድብ መሠራት አንዱ ሞዕራፍ ነው። ወንዙ ግን የኢትዮጵያ ልብ ውስጥ ከፍተኛ፣ ሚና ያለው የሶሺዮ - ፖለቲካ መገለጫ፣ የኢትዮጵያ ማንነትና ባህል ጋር ከፍተኛ ቁርኝት ያለው ነው'' ሲሉ የውጭ ጉዳዮች ኢንስትቲዩት ምክትል ዳይሬክተር አብዲ ዘነበ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ኃላፊ አረጋዊ በርሄ (ዶ/ር) በበኩላቸው፡-
''አባይ፣ በአፍሪካ ትልቁ ግድብን መገደብ ከተቻለ፣ ሌሎች ግድቦችን ለመገንባት የሚያግደን ምንም ነገር የለም።''
የታላቁ የህዳሴ ግድብ ተጠናቆ በይፋ መመረቁን መሠረት አድርገን ከውጭ ዕርዳታ ውጪ በሰፋ የህዝብ ተሳትፎ መሠራቱ ያለው አንድምታና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች በሰፊው እንዳስሳለን። የሶቨርኒቲ ሶርስስ ፕሮግራም አቅራቢው፣ የውጭ ጉዳዮች ኢንስትቲዩት ም/ዳይሬክተር ዶ/ር አብዲ ዘነበ እና የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ኃላፊ አረጋዊ በርሄ (ዶ/ር) በተጨማሪም የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ የውሃ ቴክኖሎጂ ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ኢንጂነር ታምሩ ተሠማ (ዶ/ር) እና በስፔስ ስሳይንስና ጂኦስፓሻል ተቋም የዲጂታል ኢሜጅ ፕሮሰሲንግ ሊድ ኤክስኪዩቲቭ ተስፋዬ ዳኜ ድሪባን ጋብዟቸው በጥልቀት አወያይቷቸዋል።

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsAfripodsDeezerPocket CastsPodcast AddictSpotify
አዳዲስ ዜናዎች
0