ደቡብ አፍሪካ እስራኤል ኳታር ላይ የፈፀመቸውን ጥሰት አወገዘች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱደቡብ አፍሪካ እስራኤል ኳታር ላይ የፈፀመቸውን ጥሰት አወገዘች
ደቡብ አፍሪካ እስራኤል ኳታር ላይ የፈፀመቸውን ጥሰት አወገዘች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 10.09.2025
ሰብስክራይብ

ደቡብ አፍሪካ እስራኤል ኳታር ላይ የፈፀመቸውን ጥሰት አወገዘች

በኳታር ዶሃ በንፁሃን ዜጎች ህንፃ ላይ በእስራኤል የተፈፀመው ጥቃት ዓለም አቀፍ ሕግና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት የሚጥስ ነው ሲል የደቡብ አፍሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

ጥቃቱ የሃማስ ፖለቲካ ቢሮ ልዑኮችን ዒላማ አድርጓል ቢባልም የንፁሃንን ደህንነት አደጋ ላይ የጣለ ነው ሲልም አክሏል፡፡

"ይህ የኳታርን የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት በግልፅ የጣሰው ጥቃት፤ በጋዛ የተኩስ አቁም እንዲደረስ ወሳኝ የማመቻቸት ሚናን እየተጫወተ ከሚገኘው የኳታር መንግሥት ጥረት ተቃራኒ ነው" ሲል ሚኒስቴሩ ጠቁሟል፡፡



ለኳታር ድጋፏን የገለፀችው ደቡብ አፍሪካ፤ ለሰላማዊ ንግግሮች የእስራኤል ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንዲቆም በማሳሰብ፤ በጋዛ አስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ጥሪ አቅርባለች፡፡

የደቡብ አፍሪካ መግለጫ የአረብና የእስያ ሀገራትን ጨምሮ እንደ አፍሪካ ኅብረት፣ የተባበሩት መንግሥታት እና የባህረ ሰላጤ ትብብር ም/ቤት ያሉ በርካታ የዓለም አቀፍ ተቋማትን ተቃውሞ ያስተጋባ ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0