ሩሲያ በዓለም ላይ ያለውን የዲጂታል ሥርዓት ክፍፍል እንዲቀንስ ጥረቶችን እያደረገች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒሰቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ
13:35 07.09.2025 (የተሻሻለ: 13:44 07.09.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሩሲያ በዓለም ላይ ያለውን የዲጂታል ሥርዓት ክፍፍል እንዲቀንስ ጥረቶችን እያደረገች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒሰቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ በዓለም ላይ ያለውን የዲጂታል ሥርዓት ክፍፍል እንዲቀንስ ጥረቶችን እያደረገች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒሰቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ
ማሪያ ዛካሮቫ እንዳሉት፣ በርካታ አገሮች እንደ ዲጂታል እኩልነት አለመኖር፣ በመሠረተ ልማት ዝርጋታ እና በሳይበር ደህንነት ኋላ ቀርነት ያሉ ችግሮች እያጋጠሟቸው ነው፡፡
ዛካሮቫ አክለውም “ዘላቂነት ባለው ዓለም አቀፍ ዕድገት እና እያደገ ባለው ዓለም አቀፍ የዲጂታል ተወዳዳሪነት ውስጥ የብሔራዊ ኢኮኖሚዎችንውጤታማነት ለማሳደግ በእነዚህ ዘርፎች ትብብርን ማሳደግ ያስፈልጋል” ብለዋል።
ከዚህ አንጻር ሩሲያ የሚከተሉትን ነገሮች ተቃውሞን ትደግፋለች፦
ያልተገባ የንግድ ከለላ መስጠት፣
ፖለቲካዊ ተነሳሽነት ያላቸው ገደቦች እና
ቴክኖሎጂዎችን፣ ዲጂታል አገልግሎቶችን፣ ምርቶችን እና ግብዓቶችን የማግኘት እንቅፋቶች፡፡
ዛካሮቫ እንዳብራሩት እንዲህ ያለው አቋም ለጋራ ደህንነት እና ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማፋጠን ይረዳል፤ እንዲሁም አሁን በየቦታው እየተስፋፉ ያሉ ግብይትን የማያካትቱ የፉክክር ዘዴዎችን ለመከላከል ይረዳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X