ወጣቶችን ለአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት እንዲሠሩ ያነሳሳ የፈጠራ ውድድር

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱወጣቶችን ለአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት እንዲሠሩ ያነሳሳ የፈጠራ ውድድር
ወጣቶችን ለአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት እንዲሠሩ ያነሳሳ የፈጠራ ውድድር - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.09.2025
ሰብስክራይብ

ወጣቶችን ለአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት እንዲሠሩ ያነሳሳ የፈጠራ ውድድር

በፈጠራ መር የአግሮኢኮሎጂ ሥራ ፈጣሪዎች ላይ ያተኮረ እና “ምግቤ አፍሪካዊ ነው / ምግቤ ኢትዮጵያዊ ነው” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ የግብርና ውድድር በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡ 72 አመልካቾች ከ11 ክፍለ ከተሞች የተሳተፉ ሲሆን 43 ለየት ያሉ ሐሳቦች ቀርበውበታል።

“ወደ አባቶቻችን የምግብ ሥርዓት እንመለሳለን” ሲል  የውድድሩ አሸናፊ የአግሪኢኮሎጂ ባለሙያው ክሩቤል ኃይለሥላሴ ተናግሯል።

ከፍተኛውን ውጤት ያስመዘገቡት ሦስት የፈጠራ ሥራዎች የገንዘብ ሽልማት ያገኙ ሲሆን፣ ሁሉም ለቀጣይ ድጋፍ እና ለወደፊት ዕድሎች ግምት ውስጥ ይገባሉ።

በውድድሩ የቀረቡ ቴክኖሎጂዎች ተግባር ላይ ከዋሉ፣ በአገሪቱ ውስጥ ያሉ የግብርና ተግዳሮቶች ከ70 እስከ 86 በመቶ ሊፈቱ ይችላሉ ተብሏል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0