ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 233 ቢልዮን ብር ወጪ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ
14:55 06.09.2025 (የተሻሻለ: 15:04 06.09.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 233 ቢልዮን ብር ወጪ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 233 ቢልዮን ብር ወጪ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ
ከተጠቀሰው ገንዘብ ውስጥ 223 ቢልዮን ወይም 91 በመቶ የሚሆነው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተገኘ መሆኑን የኮርፖሬት የኮሙኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር ሞገስ መኮንን የግድቡ ምርቃትን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል።
ለግድቡ ግንባታ በአጠቃለይ ከወጣው ወጪ፦
ከመላው ኢትዮጵያዊያን በቦንድ ግዢ 18.9 ቢልዮን ብር፣
በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን 1.6 ቢልዮን ብር፣
በስጦታ 3.2 ቢልዮን ብር የተገኘ መሆኑን አንስተዋል።
በግንባታው ወቅት የነበሩ የፋይናንስና የዲፕሎማሲ ጫናዎችን ተቋቁሞ በራስ አቅም የመልማት ዕድልን መወሰን የተቻለበት እንደሆነ ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X