ብሪክስ ውድድሮችን ቢያዘጋጅ አባል ሀገራቱ የልምምድ ልውውጥ ማድረግ ያስችላቸዋል - የስፖርት ጋዜጠኞች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱብሪክስ ውድድሮችን ቢያዘጋጅ አባል ሀገራቱ የልምምድ ልውውጥ ማድረግ ያስችላቸዋል - የስፖርት ጋዜጠኞች
ብሪክስ ውድድሮችን ቢያዘጋጅ አባል ሀገራቱ የልምምድ ልውውጥ ማድረግ ያስችላቸዋል - የስፖርት ጋዜጠኞች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.09.2025
ሰብስክራይብ

ብሪክስ ውድድሮችን ቢያዘጋጅ አባል ሀገራቱ የልምምድ ልውውጥ ማድረግ ያስችላቸዋል - የስፖርት ጋዜጠኞች

"እንደዚህ አይነት ውድድሮች በቀላሉ የሚገኙ ከሆነ የእኛ ሀገር የታዳጊም ይሁኑ የክለብ ቡድኖች 'ኤክስፖዠር'ን ያገኛሉ... ስለዚህ ብሪክስ ውድድሮችን ቢያዘጋጅ ትልቅ ነገር ነው ... ከዚያ ውጭ የልምድ ልውውጦች ሊኖሩ ይችላሉ። ለምሳሌ ሩቅ ሳንሄድ እዚሁ አፍሪካ ውስጥ የብሪክስ አባል ሀገራት አሉ።" ሲል የስፖርት ጋዜጠኛ ኦምና ታደለ ለስፑተኒክ አፍሪካ ተናገሯል፡፡

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ከሚፈተንባቸው አንዱ የትስስርና የጨዋታ እድሎችን የማጣት ጉዳይ ነው የሚለው ሌላኛው የስፖርት ጋዜጠኛ ልዑል ታደሰ ራስን ከዓለም ጋር ማስተሳሰር ወሳኝ ነው ሲል ይገልፃል፡፡

"በዚያ ዘርፍ (በስፖርት) ከእኛ የተሻሉ ሀገራት እስከሆኑ ድረስ ከእነ ደቡብ አፍሪካ፣ ብራዚል አሰልጣኞቻችንን የማሰልጠን እድል ልናገኝ እንችላለን፣ ለተጫዋቾቻችንም ክለቦችን ልናገኝ እንችላለን። ጥሩ ነገር ነው።" ሲልም አስረድቷል፡፡

አፍሪካውያን ስፖርትን ኢ-ፍትሐዊነትን ለመታገል ተጠቅመውበታል፣ በአኅጉሪቱ ያለው አሁናዊ እንቅስቃሴ ግን መሻሻል ይኖርበታል ሲሉም ጋዜጠኞቹ አንስተዋል፡፡

በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0