የሩሲያ የአልማዝ አምራች አልሮሳ ከአንጎላ መውጣቱን ተከትሎ ወደ ዚምባብዌ ፊቱን አዙሯል
19:37 04.09.2025 (የተሻሻለ: 19:44 04.09.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ የአልማዝ አምራች አልሮሳ ከአንጎላ መውጣቱን ተከትሎ ወደ ዚምባብዌ ፊቱን አዙሯል
አልሮሳ በአንጎላው የካቶካ ማዕድን የነበረውን የ41 በመቶ ድርሻ ከሸጠ በኋላ ሥራውን ወደ ዚምባብዌ ማዞሩን ዋና ሥራ አስፈፃሚው ፓቬል ማሪኒቼቭ በምስራቃዊ ኢኮኖሚ ፎረም ላይ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
አልሮሳ እ.ኤ.አ በ2019 በሀገሪቱ ያስጀመረውን የሥነ-ምድር ፍለጋ ስራውን ቀጥሏል ሲሉም ገልፀዋል። ኢንቨስትመንት ማስፋፋት የሚያስችሉ ጥሩ ውጤቶች ይጠበቃሉ ሲሉም አክለዋል።
አልሮሳ አሁን ላይ በአፍሪካ 40 ልዩ ፍቃድ እንዳለው ያነሱት ሥራ አስፈፃሚው፤ ተጨማሪ የአልማዝ እና ሌሎች ማዕድናት ክምችት ለማግኘት እየሠራ ነው ብለዋል።
"ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ሞዛምቢክ፣ ናሚቢያ እና ደቡብ አፍሪካ ጋር የረጅም ጊዜ ትብብር አለን። የአልማዝ ፍሰትን ለመቆጣጠር ውጤታማ ስርዓት ለመዘርጋት እገዛ እያደረግን ነው" ሲሉ ማሪኒቼቭ ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X