40 የመንግሥት ድርጅቶች በ2017 በጀት ዓመት ከሁለት ትሪሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኙ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ40 የመንግሥት ድርጅቶች በ2017 በጀት ዓመት ከሁለት ትሪሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኙ
40 የመንግሥት ድርጅቶች በ2017 በጀት ዓመት ከሁለት ትሪሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኙ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 04.09.2025
ሰብስክራይብ

40 የመንግሥት ድርጅቶች በ2017 በጀት ዓመት ከሁለት ትሪሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኙ

ድርጅቶቹን የሚያስተዳድረው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ በበጀት ዓመቱ ከታክስ በፊት የተጣራ 262.7 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማግኘት መቻሉን አስታውቋል።

ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ88 በመቶ እድገት ማሳየቱንም ገልጿል።

ለተገኘው ከፍተኛ ገቢ ቀዳሚ ድርሻ ያላቸው ዘርፎች፦

ትራንስፖርት (66.8 በመቶ)፣

የፋይናንስ አገልግሎት (14.95 በመቶ )፣

የቴሌኮምና የኃይል ዘርፍ ( በጋራ 10.08 በመቶ)።

በ2018 በጀት ዓመት 2.75 ትሪሊዮን ብር አጠቃላይ ገቢ እና ከታክስ በፊት 412 ቢሊዮን ብር ትርፍ ለማስመዝገብ ማቀዱን አስታውቋል።

ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ በ2.5 ቢሊዮን ዶላር የማዳበሪያ ፋብሪካ ለማቋቋም ከዳንጎቴ ግሩፕ ጋር መፈራረሙ የሚታወስ ነው።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0