- Sputnik አፍሪካ, 1920
Sovereignty Sources
ዓለም በሉላዊነት ምክንያት ስትተሳሰር ፤ ፕሮግራሙም አፍሪካ ባላት እምቅ የተፈጥሮ ኃብት፣ በማደግ ላይ ባለው የሕዝብ ቁጥሯ ፣ በወጣት ኃይሏ እና በአህጉሪቱ ባሉ አዳዲስ ግኝቶችና የመፍትሄ ሃሳቦች ያላትን የመወዳደር አቅምና ጥቅም በሰፊው ይዳስሳል፡፡ እንኳን ወደ 'ሶቨርኒቲ ሶርስ' ፕሮግራም በደህና መጡ፣

የኢትዮጵያ የጤና ስርዓት ወደ ቱሪዝም መዳረሻነት የመለወጥ ተስፋዎች

የኢትዮጵያ የጤና ስርዓት ወደ ቱሪዝም መዳረሻነት የመለወጥ ተስፋዎች
ሰብስክራይብ
“የጤና ስርዓት ቱሪዝምን መገንባት አስፈላጊ ነው ምክንያቱም የሰው ኃይልን መገንባት ስለሚኖርብን። ብዙ ሙያተኞቹን እያበቃን ነው። ብቃት ያላቸው በርካታ ሀኪሞች እየተፈጠሩ በመሆናቸው በየቦታው ሙያቸውን ተግባራዊ እያደረጉ ይገኛሉ። ስለዚህ መሠረተ ልማቶችና ማዕከላት ለጠቅላላ ሀኪሞችና ስፔሻሊስቶች ምቹ ከሆኑ የጎረቤት ሀገራትን ጨምሮ በርካታ የውጭ ዜጎችን ለህክምና እንዲመጡ ማድረግ ይቻላል" ብለዋል የኢትዮጵያ ጋስትሮኢንትሮሎጂ ማኅበር ኤክስኪዩቲቭ ኮሚቴ ዋና ፀሃፊው ዶ/ር ካሳ ታምሩ።
በርካታ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ዜጎች በተለይም እንደ ጅቡቲ፣ ሱዳንና ሶማሌ ላንድ ያሉት የተሻለ ህክምና ለማግኘት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ኢትዮጵያን ተመራጭ እያደረጓት ነው ።
በህክምና ቱሪዝምና ተያያዥ ጉዳዮች የሶቨርኒቲ ሶርስስ ፕሮግራም አቅራቢ የኢትዮጵያ ጋስትሮኢንትሮሎጂ ማኅበር ኤክስኪዩቲቭ ኮሚቴ ዋና ፀሃፊው ዶ/ር ካሳ ታምሩ፣ የላንሴት ሆስፒታል ማዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር አቤል ሀይሉ፣ የኦፕታልሚክ ሰርጅን ኮርኒያ የዓይን የውጭ ክፍል ህመም ሰብ - ስፔሻሊስቱ ዶ/ር ኤሌያስ እና የጠቅላላ ቀዶ ህክምና ሀኪሙ ዶ/ር መሃመድ አወል አህመድን በጥልቀት አወያይቷቸዋል።
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsAfripodsDeezerPocket CastsPodcast AddictSpotify
አዳዲስ ዜናዎች
0