የገበያ ትስስር ለአፍሪካ የሞት እና ህይወት ጉዳይ ነው ሲሉ የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት አሳሰቡ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየገበያ ትስስር ለአፍሪካ የሞት እና ህይወት ጉዳይ ነው ሲሉ የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት አሳሰቡ
የገበያ ትስስር ለአፍሪካ የሞት እና ህይወት ጉዳይ ነው ሲሉ የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት አሳሰቡ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 02.09.2025
ሰብስክራይብ

የገበያ ትስስር ለአፍሪካ የሞት እና ህይወት ጉዳይ ነው ሲሉ የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት አሳሰቡ

“ያለ ግዙፍ ገበያ፣ ማደግ አይቻልም” ሲሉ ፕሬዝዳንት ዩሪ ሙሴቪኒ የሀገሪቱ ልማት ባንክ ባሰናዳው የኡጋንዳ የፋይናንስ ልማት ጉባዔ ላይ ተናግረዋል፡፡

ትክክለኛ ልማት ለማምጣት እና ወደ አንድ የገበያ ስርዓት ለመግባት የአፍሪካ ሀገራት ከንግግር ባለፈ ወደ ተግባር እንዲገቡ አሳስበዋል፦

🟠 በአመራር ውስጥ ራዕይንና ታማኝነትን ማሳደግ፣

🟠 ጥገኛ ያልሆነ ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለትን መፍጠር፣

🟠 በሀገር ውስጥ የማይቀነባበር የሀብት ብዝበዛን ማስቆም፣

🟠 እንደ ኡጋንዳ ልማት ባንክ ያሉ በትርፍ የሚመሩ ሳይሆን ለምርታማነት ድጋፍ የሚያደርጉ ተቋማትን መገንባት፡፡

“አንድ ኪሎ ቡና አምርተህ 2.5 ዶላር ታገኛለህ፡፡ ሌላው ሰው ወደ ኔስካፌ ለውጦ በ40 ዶላር ይሸጠዋል፡፡ ማነው ረጂው? አንተ ነህ ረጂው፤ ግን ይህን አታውቀውም” ሲሉም ቁጭታቸውን ገልፀዋል፡፡

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየገበያ ትስስር ለአፍሪካ የሞት እና ህይወት ጉዳይ ነው ሲሉ የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት አሳሰቡ
የገበያ ትስስር ለአፍሪካ የሞት እና ህይወት ጉዳይ ነው ሲሉ የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት አሳሰቡ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 02.09.2025
አዳዲስ ዜናዎች
0