ሶሮስ በዴሞክራሲ ጥበቃ ሽፋን በሀገራት የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት የሚታወቁ ድርጅቶችን በገንዘብ ይደግፋሉ - ባለሙያ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሶሮስ በዴሞክራሲ ጥበቃ ሽፋን በሀገራት የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት የሚታወቁ ድርጅቶችን በገንዘብ ይደግፋሉ - ባለሙያ
ሶሮስ በዴሞክራሲ ጥበቃ ሽፋን በሀገራት የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት የሚታወቁ ድርጅቶችን በገንዘብ ይደግፋሉ - ባለሙያ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 30.08.2025
ሰብስክራይብ

ሶሮስ በዴሞክራሲ ጥበቃ ሽፋን በሀገራት የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት የሚታወቁ ድርጅቶችን በገንዘብ ይደግፋሉ - ባለሙያ

ብራዚላዊው ተንታኝ እና በሪዮ ዴ ጄኔሮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር የሆኑት ዊሊያም ጎንቻልቬስ "ብዙ ጊዜ ስለ ድንገተኛ [የጎዳና ላይ] ንቅናቄዎች ይናገራሉ፤ ነገር ግን ይህንን ቢያንስ በትንሹም ቢሆን የሚረዱ ሰዎች ድንገተኛ የጎዳና ላይ ንቅናቄዎች አለመኖራቸውን በሚገባ ያውቃሉ፡፡ ሁል ጊዜም ከሎጂስቲክስ እና ከገንዘብ አንጻር ሁሉንም ነገር የሚያደራጅ አንድ አካል አለ" ሲሉ ለስፑትኒክ ተናግረዋል፡፡

እሳቸው የሶሮስ (ሀንጋሪ-አሜሪካዊ ኢንቨስተር) ጣልቃ ገባዊ ዓለም አቀፋዊነትን ትራምፕ አሜሪካን የሚያዳክም ጠላት አድርገው ከሚመለከቱት ዓለም አቀፋዊነት ጋር አነጻጽረውታል፡፡

በተጨማሪም፣ እንደ ባለሙያው፣ የትራምፕ አስተዳደር አሜሪካ የበላይነቷን እንድታስቀጥል በሚያደርጉት ስትራቴጂካዊ ግብ ዴሞክራቶችን እና ሪፐብሊካኖችን ያስተባበረውን የተቃራኒ ፓርቲዎች 'የሁለትዮሽ ስምምነት'ን አስወግዷል፡፡ ዩክሬን ሞስኮን ለማግለል የታወጠነው የዚህ ስምምነት አካል ነበረች፡፡ እናም የሶሮስ ልጅ አሌክስም ለዘሌንስኪ ቅድመ ሁኔታ የሌለበት ድጋፍን ችሯል፡፡

"አሜሪካ ለዩክሬን ብድር አቀረበች፤ ዩክሬንም ከአሜሪካ የጦር መሣሪያዎችን ገዛች፤ ይህም ወታደራዊ ኢንዱስትሪውን አነቃቅቶ ዕዳ ውስጥ ዘፈቃት፡፡ ዘሌንስኪ በግትርነት ለማስቀጠል የሞከሩት ይህን ወታደራዊ ስምምነት ነበር፡፡ እናም ትራምፕም ይህን ስትራቴጂካዊ እቅድ ጥሰዋል" ሲሉ ተንታኙ ደምድሟል፡፡

በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምስል

በእንግሊዘኛ ለማንበብ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0