አልጄሪያው ፕሬዝዳንት ተቡኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ናዲር ላርባዊን አባረሩ
13:13 29.08.2025 (የተሻሻለ: 13:14 29.08.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አልጄሪያው ፕሬዝዳንት ተቡኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ናዲር ላርባዊን አባረሩ
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ሺፊ ግሪብ ጊዜያዊ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው መሾማቸውን የለወጡን ምክንያት ሳይገልጽ የፕሬዝዳንቱ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል፡፡
የቀደሞ የሕግ ባለሙያ ላርባዊ፣ በተለያዩ ሀገራት እና በተባበሩት መንግሥታት የአልጄሪያ አምባሳደር በመሆን ከሠሩ በኋላ ከሕዳር 2023 ጀመሮ በጠቅላይ ሚኒስትርነት አገልግለዋል፡፡
አዲሱ ተሿሚ ግሪብ፣ ከጊዜያዊ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ሥራቸው ጋር የኢንዱስትሪ ሚኒስትርነት ሥራቸውንም ደርበው ይሠራሉ፡፡የአልጄሪያ ኳታር ስቲል ኩባንያ ሊቀመንበርን ጨምሮ በተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊነቶች ሠርተዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X