ኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነቴን ሰኔ 30፣ 2018 አውጃለሁ አለች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነቴን ሰኔ 30፣ 2018 አውጃለሁ አለች
ኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነቴን ሰኔ 30፣ 2018 አውጃለሁ አለች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 27.08.2025
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነቴን ሰኔ 30፣ 2018 አውጃለሁ አለች

ሁሉም ክልልና የከተማ አስተዳደር ለሰብዓዊ ድጋፍ አገልግሎት የሚያስፈልገውን ሜትሪክ ቶን እህል እስከ ዞንና ወረዳ ድረስ እንዲይዝ እየተሠራ እንደሆነ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

ክልሎች ለፌዴራል መጠባበቂያ የሚሆን ምርት አምርተው ለመስጠት ከፌዴራል መንግሥት ጋር ውል ገብተዋል። ለዚህም ለቅድመ ፋይናንስ 3 ቢሊየን ብር ሊተላለፍላቸው መታቀዱን የኮሚሽኑን ኃላፊ ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ጋዜጣ ዘግቧል።

ኮሚሽኑ ከዚህ በፊት 70 ከመቶ የሚሆነው ሰብዓዊ ድጋፍ የሚሸፈነው በማህበረሰቡ ነው ማለቱንም ዘገባው አስታውሷል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0