ከአንድ ዓመት ገደማ በኋላ የሱዳን ከተሞች የሰብዓዊ እርዳታ ማግኘት እንደጀመሩ ዩኒሴፍ አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱከአንድ ዓመት ገደማ በኋላ የሱዳን ከተሞች የሰብዓዊ እርዳታ ማግኘት እንደጀመሩ ዩኒሴፍ አስታወቀ
ከአንድ ዓመት ገደማ በኋላ የሱዳን ከተሞች የሰብዓዊ እርዳታ ማግኘት እንደጀመሩ ዩኒሴፍ አስታወቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 26.08.2025
ሰብስክራይብ

ከአንድ ዓመት ገደማ በኋላ የሱዳን ከተሞች የሰብዓዊ እርዳታ ማግኘት እንደጀመሩ ዩኒሴፍ አስታወቀ

በደቡባዊ ሱዳን ሁለት ከተሞች ከ120 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ከወራት ከበባ እና እየተባባሰ በመጣው የምግብ እጥረት ምክንያት አስቸኳይ እርዳታ ያስፈልጋቸው እንደነበር በድርጅቱ መግለጫ ተነቧል።

በተመሳሳይ በሀገሪቱ ሰሜናዊ ምዕራብ ክፍል በሚገኘው የሰሜን ዳርፉር ግዛት ግጭቱ እየተባባሰ መጥቷል። የተመድ የሰብዓዊ እርዳታ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት (ኦቻ) በከበባ ውስጥ ባለችው የግዛቲቱ ዋና ከተማ አል ፋሽር፤ ጠለፋ እና ታጠቂዎች የሚፈፅሟቸውን ጥቃቶች ተከትሎ አንድ ሺህ በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎች ከተፈናቃዮች ካምፕ ሸሽተዋል ብሏል።

በሰሜን ዳርፉር በምትገኘው ሌላኛው ከተማ መሊት የተከሰተው ረሃብ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። በቅርብ ጊዜ የተደረጉ ግምገማዎች እንደሚያሳዩት ከሶስት ህጻናት አንዱ በከፍተኛ የምግብ እጥረት ይሰቃያል።

ወሳኝ የእርዳታ አቅርቦቱን እንደሚቀጥል ቃል የገባው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፤ የደህንነት እጦት፣ የሎጂስቲክስ መሰናክሎች እና ከባድ የገንዘብ እጥረት ዋነኛ እንቅፋት እንደሆኑበት ገልጿል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0