የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሐይቅ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የዓሣ ምርት 95 በመቶ በላይ እንደሚሸፍን ተገለፀ
15:32 24.08.2025 (የተሻሻለ: 15:34 24.08.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሐይቅ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የዓሣ ምርት 95 በመቶ በላይ እንደሚሸፍን ተገለፀ
በተጠናቀቀው 2017 በጀት ዓመት ከተመረተው 5 ሺህ 895 ቶን ዓሣ፣ ከ95 በመቶ በላይ የሚሆነው ከታላቁ የሕዳሴ ግድብ ሐይቅ የተገኘ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልን ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቢሮው የእንስሳት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ብርሃኑ ኢቲቻ፣ ግድቡ ከመገንባቱ በፊት ክልሉ በዓመት ከሁለት ሺህ 400 ቶን በላይ ዓሳ ብቻ የማምረት አቅም እንደነበረው ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡ ከግድቡ ግንባታ በኋላ፦
በክልሉ በዓመት ከ10 ሺህ ቶን በላይ ዓሳ ማምረት ይቻላል፡፡
የክልሉ ዓሣ ምርት ከእጥፍ በላይ አድጓል፡፡
ወደ ሥራ ለገቡ 30 የዓሣ ማስገር ማኅበራት የሥራ ዕድል ፈጥሯል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia