ኢትዮጵያ ከዘንድሮው መኸር ከ672 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ትጠብቃለች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ ከዘንድሮው መኸር ከ672 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ትጠብቃለች
ኢትዮጵያ ከዘንድሮው መኸር ከ672 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ትጠብቃለች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.08.2025
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ ከዘንድሮው መኸር ከ672 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ትጠብቃለች

እንደ ሀገር እስካሁን 19 ሚሊዮን ሔክታር መሬት መታረሱን የግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ኢሳያስ ለማ ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡

3.3 ሚሊዮን ሔክታር መሬት በስንዴ ዘር መሸፈኑ የተገለፀ ሲሆን 2.1 ሚሊዮን ሔክታሩ በክላስተር (ኩታ ገጠም) የታረሰ ነው ተብሏል፡፡በአጠቃላይም በመኸር እርሻ 176 ሚሊዮን ኩንታል የስንዴ ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ ኢሳያስ ጠቅሰዋል፡፡

መሪ ሥራ አስፈፃሚው፣ በአሁኑ ወቅት ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው ከሆኑ አካባቢዎች በስተቀር በአብዛኛው የሀገሪቷ ክፍል ዘር መዝራት ተጠናቅቋል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0